Get Mystery Box with random crypto!

አል-ፋሩቅ islamic

የቴሌግራም ቻናል አርማ alfaruq_islamic — አል-ፋሩቅ islamic
የቴሌግራም ቻናል አርማ alfaruq_islamic — አል-ፋሩቅ islamic
የሰርጥ አድራሻ: @alfaruq_islamic
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.41K
የሰርጥ መግለጫ

«ያ አላህ! ባልሰራበት እንኳ ወደ በጎ ነገር
ያመላከተ ሰው የሚያገኘውን አጅር አታሳጣኝ፡፡»
ማሳሰቢያ:- Leave Channel ከማለቶ በፊት
ያልተመቾት ነገር ካለ ያሳውቁን!
💻
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
🍂. ሀሳብ፣አስተያየት ካሎት ☞ ✍ @All_faruq_islamic_bot

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 21:12:50 ጀነት ውስጥ ባገኘሁህ ግዜ እንዳልረሳህ ፈልጌ ነው!

በአንድ የቴሌቪዥን ጣብያ ላይ ጋዜጠኛው አንድ የናጠጠ ባለሀብትን ቃለ መጠየቅ እያደረገለት ነው።

ጋዜጠኛው፦በህይወትህ በጣም ያስደሰተህ ነገር ምንድን ነው?
ባለ ሀብቱ ፦ በህይወት ደስታን ለማግኘት አራት የተለያዩ ሙከራዎችን ሞክርያለሁ።
መጀመርያ እራሴን ለማስደሰት የምፈልገውን ነገር ሁሉ መግዛት ነበር ፤ ሆኖም ምንም አይነት ደስታ ማግኘት አልቻልኩም።

በሁለተኛው ደረጃ ደግሞ ውድ የተባሉ ነገሮችን ሁሉ በመግዛት የግሌ ማድረግ ጀመርኩ ፤ ሆኖም ከፍተኛ ገንዘብ አውጥቼ የገዛሁት ሁሉ ብዙም ሳይቆይ ፋሽኑ ያልፍበትና ደስታዬ ይጠፋል አሁንም ዘላቂ የሆነ ደስታ የለም።

በሶስተኛ ደረጃ ያለኝን ሀብት ተጠቅሜ ትላልቅ የሚባሉ ፕሮጀክቶችን ማከናወን ድርጅቶችን መግዛት ጀመርኩ ሆኖም የተመኘሁትን ያህል ደስታ ማግኘት አልቻልኩም።

በመጨረሻም አንድ ጓደኛዬ አንድ ሀሳብ አቀረበልኝ፤ ይህም የአካል ጉዳተኛ ለሆኑ ህፃናት የተወሰኑ ተንቀሳቃሽ ወንበሮችን ( ዊልቸር) ገዝቼ እንድሰጥ ነበር።
በርግጥም ጓደኛዬ የጠየቀኝን ተንቀሳቃሽ ወንበሮች ገዝቼ ሰጠሁት፤ ነገር ግን አብሬው ሄጄ ስጦታውን ለልጆቹ በእጄ መስጠት እንዳለብኝ አጥብቆ ለመነኝ እምቢ ማለቱ ከበደኝና ጥያቄውን ተቀብዬ በሀሳቡ ተስማምቼ ወንበሮቹን ለህፃናቱ በእጄ አስረከብኳቸው፣ በህፃናቱ ፊት ላይ ከፍተኛ የሆነ የደስታ ስሜት ይንፀባርቅ ነበር፤ ህፃናቱ ወንበሩ ላይ ተቀምጠው በደስታ ይቧርቁም ነበር፤ በተቻላቸው መጠን ዊልቸሩ ላይ ተቀምጠው ወደ ግራ ወደ ቀኝ በመንቀሳቀስ እየሳቁ ደስታቸው ሲገልፁ የመዝናኛ ስፍራ ውስጥ ሆነው የሚዝናኑ ይመስሉ ነበር። ነገር ግን እውነተኛ የሆነን ደስታ ልቤ ውስጥ የጫረው አንደኛው ህፃን ነበር ፤ ልወጣ ስል በእጆቹ እግሬን አፍኖ ያዘኝ፤ ቀስ ብዬ እያወራሁት እጁን ከእግሬ ለማስለቀቅ ብሞክርም ፍቃደኛ አልነበረም፤ አይኖቹ ፊቴ ላይ ተተክለው በትኩረት እየተመለከቱኝ ነው። ወደ ታች ዝቅ ብዬ፦
" ከመሄዴ በፌት ከኔ የምትፈልገው ሌላ ነገር አለን? " ብዬ ጠየቅኩት።
አስደማሚና መቼም የማልረሳውን መልስ እንዲህ ሲል ሰጠኝ፦
ህፃኑም እንዲህ አለኝ፦ "ጀነት ውስጥ ፊትህን በደንብ እንዳስታውስና አላህ ፊት ቆሜ መልሼ ላመሰግንህ ፈልጌ ነው።"

ሰደቃ በሰው ልጅ ህይወት ውስጥ ከባድ ተፅእኖ ከሚያሳድሩ የኢባዳ ዘርፎች አንዱ ነው!

https://t.me/Alfaruq_islamic
https://t.me/Alfaruq_islamic
109 viewsرب ٱشرح لي صدري ويسر لي أمري , edited  18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 21:09:07 «ለምን ደግን ነገር አልጠረጠሩም?»

አዒሻ (ረዐ) ተጓዦች ጥለዋል ሄደው ከኋላ ከቀረ አንድ መንገደኛ ጋር በመምጣቷ ምክንያት በዝሙት በታማች ጊዜ ብዙ ሰው እውነት ይሆናል ብሎ ጠረጠረ። አንዳንዶች ነቢዩን (ዐሰወ) እንዲፈቷት ጠየቋቸው። ሌሎች ደግሞ ማስረጃ እስከሌለ ድረስ ሚስታችሁን ያዙ አሏቸው። ነቢዩም (ዐሰወ) ውሳኔ ከማሳለፍ ይልቅ ዝምታን መረጡ።

በዚያን ቀን አቡ አዩብ ኻሊድ ኢብን የዚድ አል-አንሷሪ (ረዐ) ወደቤቱ ሲገባ ታዲያ ሚስቱ «ስለ አዒሻ የሚወራውን ሰምተሃል?» በማለት ጠየቀችው። አቡ አዩብም (ረዐ) «አንቺ በእሷ ቦታ ብትሆኝ ታደርጊው ነበር?» አላት። ሚስቱም «በአላህ ይሁንብኝ! በፍፁም አላደርገውም።» አለችው። አቡ አዩብም (ረዐ) «እንግዲያውስ አዒሻ ከአንቺ ትበልጣለችና በፍፁም አታደርገውም።» አላት።

በዚህ ጊዜ አላህ ቁርኣን አወረደ። እንዲህም አለ፦

«ውሸቱን በሰማችሁት ጊዜ ምእምናንና ምእምናት በጎሶቻቸው ለምን ደግን ነገር አልጠረጠሩም? ለምንስ ይህ ግልፅ ውሸት ነው አላሉም?»
(ኑር 12)

ስለምእመናን ማስረጃ ያልቀረበበት ክፉ ነገር ሲወራ «አያደርጉትም» በማለት በደግ መጠርጠር ያስፈልጋል። ክፉ ነገር ለመጠርጠር እንደምንቸኩለው ደግ ነገር ለመጠርጠርም መብት አለንና ክብራቸውን መከላከል ይገባል።

ከዚያም አላህ ቀጠለና ደግን መጠርጠር ከከበዳችሁ እንኳን ማስረጃ የሌለው ነገር ስትሰሙ ለምን ዝም አትሉም? በማለት ጠየቀ።

«በሰማችሁትም ጊዜ በዚህ ልንናገር ለእኛ አይገባንም። ጥራት ይገባህ። ይህ ከባድ ቅጥፈት ነው፤ አትሉም ነበርን?»
(ኑር 16)

እርግጥ ነው አንድ ሙእሚን በክፉ ሲታማ እኛንም የግድ ተሳተፉ ብሎ የሚያስገድደን የለምና ቢያንስ ዝም በማለት ከወንጀሉ መራቅ እንችላለን።

አንድን ሙእሚን በክፉ መጠርጠር ነገሩ ትክክል ቢሆንም አጅር የለውም። ስህተት ከሆነ ደግሞ ወንጀል ነው።

በደግ መጠርጠር ወይም ዝም ማለት ግን ነገሩ እውነትም ቢሆን ወይም ባይሆን ክብሩን መጠበቂያ ነውና አጅር አለው።

https://t.me/Alfaruq_islamic
https://t.me/Alfaruq_islamic
116 viewsرب ٱشرح لي صدري ويسر لي أمري , 18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 05:42:30 ➳ቢክራነት(ልጃገረድነት)እና ሴት እህቶቻችን



አሁን ላይ ቢክራ ( ልጃገረድ ) እንስቶች እንደ ዳይኖሰር ከምድረ ገፅ ከጠፉ ሰነባብተዋል የሚል ወሬ በረጅሙ ይናፈሳል ፡፡ ተጨባጩን ያስተዋሉ ደግሞ " የለም , ሙሉ ለሙሉ እንኳ አልጠፉም ፡፡ ባይሆን እንደኛዎቹ ዋልያዎች ብርቅዬ ናቸው " ሲሉ ይደመጣሉ ፡፡
የሆነው ሆኖ ሴቶቻችን ከዚህ በፊት የሚታወቁበት ቁጥብነትና ጨዋነት ርቋቸዋል ፡፡ በምትኩ ስርዐት አልበኝነትን መርጠው የማንም መጫወቻ እየሆኑ ነው ፡፡
ከአለባበስ ጀምሮ አካሄዳቸውንና የአነጋገር ስልታቸውን ያስተዋለ ጥሩ ተጨባጭ ላይ እንዳልሆኑ ይገለጥለታል ፡፡ ካፊሯ ላይ የማይስተዋለውን ደማማቅ ቀለማትና ሙሉ የሰውነት ቅርፅን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ቀሚስ ለብሳ አውራ ጎዳናውን የምታዥጎደጉደው የኛው እህት ነች ፡፡
አይደለም እንዴ ?
( ዋ ! አይደለም ብለህ ትዋሽና በብሎክ እንዳላሰናብትህ )
ወሏሂ ግን ሴቶችዬ በጣም እኮ ነው ያበዛችሁት ፡፡ አልታወቃችሁም አይደል ?
እንደው ጉዳችሁን እዚህ ህዝብ ፊት አልዘረግፈውም እንጂ በጣም መስመር ስታችኀል ፡፡
'
ከዚህ በፊት ቢክራነት ( ልጃገረድነት ) ትልቅ ክብር ነበረው ፡፡ እርሱን ለመጠበቅና በተገቢው ቦታ ለማኖርም ትልቅ ተጋድሎና ትንቅንቅ ይደረግ ነበረ ፡፡ አሁን ግን አንዲት እንስት ቢክራነቷን በሶስት ኪሎ ስኳር እንዳትቀይር ሁላ ይስሰጋል ፡፡ በቃ እንደውም አንዳንድ ቦታዎች ላይ ቢክራነት እንደፋርነት ሁላ እየተቆጠረ ነው ፡፡ አጂብ !
ታላቋን የምዕመናት ሞዴል የዒሳ ዐለይሂ ሰላም እናት የሆነችው መርየም ዐለይሃ ሰላም ዝንተ ዐለም በቁርዐን ስትወደስ የምትኖረው ቢክራ ስለነበረች እንጂ ከቶስ ሌላ ለምንድነው ?
ጌታችን አልሏህ ﷻ መርየም ዐለይሃ ሰላምን አስመልክቶ በተከበረው ቃሉ ( ቁርዐን ) እንዲህ ሲል እስከ ዕለተ ቂያማ የሚዘከርን ውዳሴ አውርዶላታል
'
وَإِذْ قَالَتِ ٱلْمَلَٰٓئِكَةُ يَٰمَرْيَمُ إِنَّ ٱللَّهَ ٱصْطَفَىٰكِ وَطَهَّرَكِ وَٱصْطَفَىٰكِ عَلَىٰ نِسَآءِ ٱلْعَٰلَمِينَ
.
መላእክትም ያሉትን ( አስታውስ ) ፡፡ « መርየም ሆይ ! አላህ በእርግጥ መረጠሽ ፡፡ አነጻሽም ፡፡ በዓለማት ሴቶችም ላይ መረጠሽ ፡፡ »
ሱረቱ አል ዒምራን 42
'
እነዚህ " ፋራ " ባይ ሰገጤዎች ያልተረዱት አንድ ትልቅ ቁም - ነገር አለ ፡፡ እርሱም ዛሬ ላይ ቢክራነቷን ጠብቃ የጨዋነት አክሊልን የሙጥኝ ያለችው እህት ልክ እንደሌሎቹ " አተራማሽ " እንስቶች የፈለገችውን ማድረግ ትችላለች ፡፡
አትችልም ?
ቀላል እኮ ነው ፡፡ ነገር ግን ያቺ ክብሯን ለማንም ወፈፌ ሲሳይ ያደረገችው እህት ግን ዳግም ክብሯን ልመልስ ብትል ሰማይ ትቧጥጣታለች እንጂ #ሙስተሂል ነው ፡፡
እና ታድያ ፋራው ማን ነው ?
'
እህ .... ቢክራ ሆኜ ምን አደርግበታለሁ ( ? ) ካልሽ , ያልገባሽ ሌላ ተጨማሪ ትልቅ ቁም ነገር አለ ማለት ነው ፡፡ እርሱም , አብዝሃኛው የሙስሊም ወንዶች ለቢክራነት የሚሰጡት ትኩረት በጣም የተለየ ነው ፡፡ ምንም እንኳ ከዚህ ቀደም የስድስት እንስትን ቢክራነት የገረሰሰ ቢሆንም ትዳር ሲያስብ ግን ማንም ያልተጨማለቀባትን ንፁኀን ቢክራዋን ይመኛል ፡፡ ለምን ( ? ) ስትዪው .... ኧረ ማንም የተጨማለቀባትን እኔ ምን ልትሰራልኝ ብሎ በድፍረት ይመልስልሻል ፡፡
በአጭሩ ምን ልልሽ ፈልጌ መሰለሽ .. ቢክራነትሽን እንደ ቀልድ ካስረከብሽ በኀላ የትዳርሽ ጉዳይ ፍፁም አሳሳቢ ይሆናል ፡፡ ውጫዊ ገፅታሽን ተመልክቶ ለትዳር ሲመለምልሽ በመጀመሪያ የሚጠይቅሽ ቢክራነትሽን ነው ፡፡

ባለማወቅም ሆነ በማወቅ ይህን ቢክራነት ካጣን ለሚመጣው ወንድ
ለትዳር ያለውን ነገር በግልጽ መነጋገር
መልካም ነው።

ቢክራ ነኝ ብዬ ሸውጄ አገባዋለሁ ... ብለሽ እንዳታስቂኝ ፡፡ እህቴ ስንቶች ይህንን የጅል ቀመር ተጠቅመው አበሳቸውን እያዩ መሰለሽ ፡፡ ቢክራ መሆኗን ተናግራ ከተጋባች በኀላ ባል ሆዬ ፈልጎ ሲያጣ ሚስት ላይ ከፍተኛ ጫናና የጥላቻ ስሜት ማንፀባረቅ ይጀምራል ፡፡ ባገኘው አጋጣሚም ሞራሏን የሚያደቅበትንና ቂሙን የሚበቀልበትን ሁኔታዎች ያመቻቻል ፡፡ እንደውም አንዳንዱ በዚያው የመጀመሪያ የጫጉላ ምሽት " አይንሽን ላፈር ካጠገቤ ዞር በይ " ይላል።

አላህ ትክክለኛውን መንገድ ይምራን
መልካምን ነገር ከሚያወሩት ሳይሆን
ከሚተገብሩት ያርገን።
ጆይን
https://t.me/Alfaruq_islamic
https://t.me/Alfaruq_islamic
11 viewsرب ٱشرح لي صدري ويسر لي أمري , 02:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:58:38 ┏─━─━─━∞◆∞━─━─━─┓
". #ፊትና ".
✎ፀሐፊ፦ ፎዝያ ፈይሳ
┗─━─━─━∞◆∞━─━─━─┛
┎━─━─━─━─━─━─━─━─━┒
. በ al faruq Islamic የተዘጋጀ .
. ልብ አንጠልጣይ ታሪክ.
┖━─━─━─━─━─━─━─━─━┚
{ክፍል 15የመጨረሻዉ ክፍል}

<<ሀቢልዬ አትፍረድበት ጓደኝነታችንን ታዉቀዉ የለ ስለምነዉ ነዉ ወደ አንተ እንደምመለስ ስነግረዉ የተስማማዉ ደሞ ልጅቷን አንቀህ ልትገላት እንደነበር ሰማሁ ግን እንደዛ ማድረግ አልነበረብህም ምክንያቱም ሰዎች ሲያጠፉብህ ለአፉታ ቅርብ መሆን መቻል አለብህ
<የኔ ዉድ የሷ ግን በዛ ከሂወቴ እንድትወጣ ነግሬአት አስጠንቅቄአት ነበር ነገር ግን በአንቺ መጣችብኝ እናም ተበሳጨሁ ለዛ ነዉ
<<ለማንኛዉም እሺ በቃ ሁለተኛ ትቼህ አልሄድም እና ወንድምህስ
<ከሱ ጋር የተለያየነዉ ያኔ አንቺ የሄድሽ ጊዜ ነበር ከቤት አባርሬዉ ስመለስ ያጣሁሽ
<<እንዴ ለምን
<እሱ የራሱን ሂወት መርጧል ስለዛህ ከኛ ትእዛዝ ከወጣ ደሞ እቤት ምንም አይሰራም ስለዛህ ነገር ደሞ እንርሳዉ ብዬ የባልና ሚስት ልፊያ ጀመርን ሁስኒ ከልቧ ነበር የተደሰተችዉ አልሀምዱሊላህ።

"""ቆይ እናንተ ሚስቴ ታማ የራሳችሁን ወሬ ታወራላቹንዴ
<አንተ ሀቢል ደሞ ምንድ ነዉ የምትለን ያዉ ሀኪም ቤት ይዘናት ልንሄድ ነዉ ከሂባ ጋር እናስመረምራታለን
<<ቆይ እኔስ
<አንተም ትመጣለህ
<<ያዉ አንተ የምትመጣ ከሆነ ሂባ ቤት ቁጭ ብላ ትጠብቀን
<አይ አይ አይሆንም
<<እንዴ ሀሱ ለምን አይሆንም
<እዚ ሰፊ ቤት እኛ ሆስፒታል ደርሰን እስክንመጣ ድረስ ብቻዋን ትፈራለች
<<እንዴ ሀሱ
<እ ምን ልትል ነዉ አንተ ለሚስትህ ብቻ ነዉዴ የምታስበዉ ብሎኝ ተኮሳተረ ገባኝ ለካ ሀሱ ከሂባ ድብን ያለ ፍቅር እንደያዘዉ መናገሩ ከብዶታል ሂባ በጭቅጭቃችን አንገቷን ደፍታ ትስቃለች በዚህ ጊዜ ሚስቴ መታ ሀቢል ብላኝ በቆምኩበት ተደገፈችኝ ና ሀኪም ብት መሄድ አያስፈልገዉም ብላ እጇን በሆዷ ይዛ ሀቢልዬ የልጅ አባት ለመሆን ተዘጋጅ ብላኝ ፈገግ አለች ያለቢ በሀያቴ እንደዚች ቀን ተደስቼ አላዉቅም አልሀምዱሊላህ ብዬ የሚስቴን ግንባር ስሜ በጣም እንደማፈቅራትና ሁሌም ሰበብ ሆኜ እንደምጠብቃት ነገርኳት በዚህን ጊዜ ሂባና ሀሱ በኔ ንግግር አጨበጨቡልንና ሀሱ እኔና ሂባም እንፈልጋቹሀለን ብለዉ ከመጅሊሱ ለይ አስቀመጡንና ሁለቱም በቲኒሹ ተራርቀዉ ተቀመጡ እኔም ሂባም ሁኔታቸዉን ለመከታተል ቁጭ አልንና እሺ ሀሱ ምን ነበር ብዬ ተኮሳትሬ የኩት ሀሱ ቁም ነገር ሲያወራ በጣም ይኮሳተር ነበር ዛሬ ግን መሽኮረመሙን መርጦ የኔንም አይን ማየት እያፈረም ቢሆን መናገር ጀመረ
<ይወልህ ሀቢል አንተ ለኔ ወንድሜ ነህ ሚስትህ ደሞ የቅርብ ጓደኛዬም እህቴም ናት እናም እኔ ሂባን ስለማፈቅራት ፍቅሬን በሀላል ለማድረግ አስቤ ነበር ይሄ ስሜት ደሞ እኔ ላይ ብቻም አልነበረም ያለዉ እሷ ላይም እንዳለ አስተዉያለሁ እናም በዚ ዙሪያ ሽማግሌ ሆነህ ከጋሼ ጋር እንድትሄዱልኝ ነበር ጋሼ የሚለዉ የኔን አባት ነዉ እናም መናገሩን ቀጥላል ሁስኒ ሂባን እንደምቶጃትም አዉቃለሁ ነገር ግን በቻልኩት አቅም እንደ ንግስት ለማኖር ቃል እገባልሻለሁ እና ልትተባበሩኝ ትችላላቹ
<<ይወልህ ሀሱ እህቴን በሀላል ስለፈለካት አመሰግናለሁ ግን የሷንም ስሜት ለማወቅ ብጠይቃት ቅር አይልህማአ
<አዎ አይለኝም ጠይቂያት
<<እሺ እህቴ ትወጂዋለሽ
<አዎ እህቴ እወደዋለሁ ሀሱን እስከማገባዉ ድረስ ጊዜዉ ይናፍቀኛል ብላኝ ነገረችን ከዛም በፍጥነት ሀቢልና የሀቢል አባት የተወሰነ ሰዉ መርጠዉ ሽምግልናዉን አፍጥነዉት ሰርጉን በቶሎ አደረጉትና ተጋብተዉ መኖር ጀመሩ ከተጋቡ 4 ወር ሆናቸዉ እኔና ሀቢል ደሞ 9ወር ሆኖናል አልሀምዱሊላህ ለቼካፕ ወደ ሆስፒታል ከሀቢል ጋር እየሄድን ሀሱና ሂባ ደሞ ከዋላ በራሳቸዉ መኪና እየተከተሉን መጓዛችንን ቀጠልን ነገር ግን የሆነ መንገድ ጋር ሰዎች ተሰብስበዉ የመኪና ማለፊያ ቦታ ጠፋና ሀቢል ከመኪናዉ ወርዶ ወደ ሰዎቹ ተጠጋና ወደኔ ዞሮ አየኝ ልወርድ በሩን ስከፍት በቶሎ መጣና አትዉረጂ አንቺ ድርስ ነፍሰ ጡር ስለሆንሽ ግርግሩ ጥሩ ላይሆንልሽ ይችላል ብሎ ዘግቶብኝ ሄደ ሀሱም ተከትሎት ወደሰዎቹ ተጠጋጉ ነገር ግን ሀቢል ሲቆይ ከፍቼ ወደ ሰዎቹ ገባሁ ነገር ግን ያየሁትን ነገር ማመን ከበደኝ አዎ የሀቢል ወንድም አድናን ነዉ በጣም የተቀዳደደ ልብስ ለብሷል በዚ መሀልም ከሰዉ ተጣልቶ አፉ ደም በደም ሆኗል ሀቢል ፈዞ ከቆመ ቡሀላ እጄን ይዞ ወደ መኪናዉ ገባና ክላክስ እያደረገ ሰዎቹ ዞር እስኪሉለት ድረስ ብቻ ቆየ ከዛም ወደ ሆስፒታል ምንም እንዳልተፈጠረ ሆኖ መጓዛችንን ቀጠልን እኔ ላወራዉ ገና ይወልህ ስለዉ ይወልሽ የኔ ሚስት እባክሽን ስለወንድሜ ከሆነ አታዉሪ ይቅር ብሎ ሀኪም ቤት ደርሰን እህቴም የሶስት ወር ነፍሰጡር መሆኗን ሰምታ በደስታ አብደን እኛ ቤት ማለትም የኔና የሀቢል ቤት እራት ለመብላት መጓዝ ጀመርን ከዛም ያቺን ቀን ተደስተን አሳለፍንና ሂባም ሀሱም ወደየቤታቸዉ ሄዱ እኛም እቤታችንን ዘጋግተን ተኛን።

"ሀቢል በሩ በሀይል እየተንኳኳ ነዉኮ ተነስ ሂድና ክፈት ብላኝ ሁስኒ ስትነግረኝ እኔም እሺ ብያት ሄድኩኝ ና በሩን ከፈትኩት በሩ ጋር የቆመዉ ሀሱ ነበር ደንግጬ ምነዉ ሀሱ ችግር አለንዴ አልኩት ሀሱም ዝም ካለ ቡሀላ እጄን እየጎተተ አሶጣኝና ወደ ግራ በኩል አዞረኝ.ወንድሜ ኩርምት ብሎ ተኝቷል እኔን ሲያየኝ ተነስቶ ወደኔ መጠጋት ጀመረና አጠገቤ ቆመ
<<ምን ፈለክ
<ወንድሜ ቅጣቴን አልጨረስኩምንዴ
<<ይቅርታ ገና አልተቀጣህም
<እሺ ግን እናቴ ብትኖር ለኔ ብዙ መስዋት እንደምትከፍልልኝ አዉቅ ነበር ነገር ግን እሷ ስለሞተች አዉጥታቹ ጣላችሁኝ ብሎ አልቻልኩም በቃ ይቅር በለኝ ብሎ አቀፈኝ እኔም ስላልቻልኩ መልሼ አቀፍኩትና ወደቤት አስገባሁት ሻወር ወስዶ የኔን ልብስ እንዲለብስ ካደረኩት ቡሀላ ስለ ፍቅረኛዉ ጠየኩት እሱም በማዘን ተከዘ
<ወንድሜ አዉቃለሁ ስታሳድጉኝ በጣም አቅብጣቹሁኝ ነበር ነገር ግን ከሷ ጋር አብረን ከወጣን ጌዜ ጀምሮ እጄ ላይ ያለዙ ገንዘብ እስኪያልቅ አብራኝ ነበረች ከዛን ግን ማለቁን ስታዉቅ እኔ እንደዛች ሂባ ተብዬዋ ደደብ አፍቃሪ አይደለሁም ብላኝ ገንዘብ ወዳለበት አመራች እኔም የሙስሊሟ እህቴን ሂወት እንዳበላሸሁት የገባኝ ያኔ ነዉ ጎዳ ና ላይ መኖር ከጀመርኹ ቆይቻለሁ ነገር ግን ምን ላድርግ ወደ ቤት ለመመለስ ስራዬ አሳፈረኝ በዛ ላይ የአንተ ሚስት እህት ሂባ መሆኗን ሳስብ አፈርኩ
<<በቃ አብሽር ዋናዉ ሰላም መሆንህና ከጥፋትህ መማርህ ነዉ
<ወንድሜ ግን ሂባን ልክሳት እፈልጋለሁ አፉታም ልጠይቃት እፈልጋለሁ ብዬ ወንድሜን ስጨቀጭቀዉ ሀሱ እንዲያመጣት አዘዘዉና ሂዶ አመጣት ሀሱ ሂባን አቅፎ ነበር ይዟት የገባዉ እሷም ለይቅርታ እንደተጠራች ስለምታዉቅ አፉታ ስጠይቃት ቀለል አድርጋ አፉተሊላህ ነበር ያለችኝ እኔም ከዚ በላይ አጋጣሚ ስለማላገኝ ብዬ ሂባን ለብቻዋ ጠርቼ ወደዉጪ እንድችወጣ ኻደረኩኝ ቡሀላ የማወራት ነገር ጠፋኝ
<ሂባዬ አምሮብሻል
<<ጀዛከላህ
<ያዉ በጣም እንደጎዳሁሽ ይገባኛል ነገር ግን ልክስሽ እፈልጋለሁ
<<አላህ ከአንተ ይቅርታ በፊት ነዉ የካሰኝ
<እንደዛ ከሆነ ለምን አላገባሽምና ደስተኛ አላረግሽም እባክሽ ፍቀጂልኝ ብዬ ተንበረከኩላት
https://t.me/Alfaruq_islamic
132 viewsرب ٱشرح لي صدري ويسر لي أمري , 17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 21:16:08 ┏─━─━─━∞◆∞━─━─━─┓
". #ፊትና ".
✎ፀሐፊ፦ ፎዝያ ፈይሳ
┗─━─━─━∞◆∞━─━─━─┛
┎━─━─━─━─━─━─━─━─━┒
. በ al faruq Islamic የተዘጋጀ .
. ልብ አንጠልጣይ ታሪክ.
┖━─━─━─━─━─━─━─━─━┚
{ክፍል 14}

ልታስለቅቀኝ ብትሞክርም አልቻለችም ሰፈራችን ጭር ያለ ስለሆነ ማንም አላየኝም እኔ ግን ከሰከንድ ሰከንድ በሀይል እያነኳት መጣሁና ትንፋሿ እየተቋራረጠ በስተመጨረሻ እጄን ለማስለቀቅ መሞከሯን ትታ ፀጥ አለች እኔም ሀይል እየተጠቀምኩ ሳለ አይኗ በጣም የሰፈጥ ጀመር በመሀል የሆነ ሰዉ እጄን በሀይል ሲመታኝ ለቀኳት እሷም አሰያስነጠሰቸሰና ትንፋሿን እየሰበሰበች አጎንብሳ ለተወሰነ ደቂቃ ቆመች እጄን የመታኝ ሀሱ ነበር ኬት መጣህ ሳይባል ደርሶ መምታቱ ገርሞኝ ዝም ብዬ አፈጠጥኩበት
<አዎ አፍጥጥ ብታፈጥ እኔ አልፈራህ
<<ቆይ ለምን መታህኝ
<ልጅቷንኮ ልትገላት ነበር ይገባሀል እንዴት ነዉ ይሄ ሁሉ ጭካኔ የመጣልህ ቆይ በሴት ልጅ ላይ እጅህን ማንሳቱ ጀብድ መስሎህ ነዉዴ የታየህ ብሎ አንባረቀብኝ እኔ የሱን ጩህት ሰምቼ ወደ ሙሪዳ ስዞር እሷ የለችም ከኛ ርቃ ሄዳለች
<<ሀሱ ሙሪዳ ሂወትንኮ ነዉ የበጠበጠችዉ እና ዝም ልበላት
<አዎ ዝም በላት
<<ለምን?
<ምክንያቱም ከዚ ቀደም አብረሀት ብዙ ወንጀል ሰርተሀል ያዉም ከባድ ስለዚህ አንተ የመናገር መፍት ስለሌለህ ዝም ብትልና ሁስኒን ብትፈልግ ይሻልሀል ለማንኛዉም ቻዉ በቃ ብሎኝ ከአጠገቤ ተሰናብቶኝ ሄደ እኔ ብቸኝነቱም ሲብስብኝ ገብቼ ወደ መስገኛዬ ኡዱ አድርጌ እቀርበዉ ጀመር የኔ መሸሸጊያዬ አንድ አሏህ ብቻ ስለሆነ ሰላት ሰግጄ ለረጅም ደቂቃ ዱአ አደረኩኝ ላለፈዉ ወንጀሌም አልቅሼ ተዉበት በድጋሚ ተዉበት አደረኩኝ ዉስጤን ቅልልኝ ብሎኝ ተነሳሁና ጊቢዉ ዉስጥ መዟዟር ጀመርኩና ስለ ወንድሜ ማሰብ ጀመርኩ ብቻ ሁለታችንም ፊትና እንደገጠመን ቢገባኝም ግን ምንም ማድረግ ስላልቻልኩ በልቤ መልካም ነገር እንዲገጥመን ተመኘሁ።

""ሰአቱ እየረፈደ ነዉ አሁን 3:00 ሆኗል ሀሱ ደሞ በአስቸኳይ ቤቴ ና እፈልግሀለዉ ብሎኝ ነበር እኔም ቁጭ ብዬ ቁርስ መመገብ ጀመርኩ ብቻዬን መብላት ከጀመርኩ ድፍን አንድ ወር ሆነኝ ሁሌም የሁስኒን ስልክ ስሞክር ጥሪ አይቀበልም ሂባ ጋር ደዉዬ አዲስ ነገር ካለ ብዬ ስጠይቃት ሁሌም ምንም የለም ትለኛለች መጣላታችንን ቤተሰቦቿ ስላልሰሙ መናገሩ ደሞ ከበደኝ ብቻ ቁርሴን በልቼ ስጨርስ ወደ ሀሱ ቤት አቀናሁ ሀሱ እናትና እህቱ አብረዉት ስላሉ ከነሱ መነጠል አይፈልግም አግባ ብለዉም አይሰማኝም ብቻ ቤታቸዉ ደረስኩና ጊቢዉ ተከፍቶልኝ ገብቼ መኪናዬን አቆምኩኝና ወደ ሳሎናቸዉ ለመግባት መራመድ ጀመርኩኝና በሩን አንኳኳሁና የሀሱ እህት ከፈተችልኝ ወደ ዉሰጥ ቀጥታ ገብቼ ሳይ የማየዉ ነገር ቅዠት ነዉ ወይስ ህልም ነዉ ነዉ ወይስ እዉን ነዉ ብዬ በጣም አይኔን ማሻሸት ጀመርኩ ነገር ግን ምንም የተቀየረ ነገር የለም አዎ የለም ምክንያቱም ሚስቴ ወይም ሁስኒና እህቷ ሂባ እዚ አሉ በመገረም እዛዉ ቆሜ ሀሱን ተመለከትኩት እሱም
<ሶዬ እዛ ምን ይገትርሀል ስትፈልጋት አልነበር ይህዉ ዉሰዳት ብሎ መሳቅ ጀመረ እኔ እየሆነ ያለዉ ስላልገባኝ ሁሉንም አፈራርቄ እመለከታቸዉ ጀመር ሁስኒ ወደኔ ተጠግታ ብቸኝነቱ አልሰለቸህም የኔ ባል ብላ አቅፋ ሳመችኝ ና ወደ ቤተሰቡ ተቀላቅለን ተቀመጥን ቲኒሽ ተጨዋዉተን ሁስኒ ቤቴ ናፍቆኛል እንሂድ ብላ ስትጠይቀኝ በደስታ ተነስቼ ነይ ብዬ እጇን ይዤ ስነሳ ሂባም ተከተለችን ሀሱም ተከተለን የሂባና የሀሱ ሁኔታ አላማረኝም አይነ ዉሀቸዉ ያጠራጥራል ብቻ አይን ለአይን እየተያዩ መተፋፈርም ጭምር ጀምረዋል እናም ወደ ቤት ሄደን ከደረስን ቡሀላ እስከ ምሳ ሰአት ተጨዋዉተን ምሳ ሰአት ሲደርስ ምሳ በልተን ሰላት ሰአት ሲደርስ መስጂዱ ስለሚርቅ እዛዉ ቤት ሰግደን መጨዋወት ጀመርን ሂባ ወደ ቤት ልሂድ ብላ ተነሳች በዚ መሀል ሀሱ በቃ ልሸኛት ብሎ ተከታትለዉ ወጡ ሁስኒም በሁኔታቸዉ ሳትጠረጥር አትቀርም እነሱ ከመሄዳቸዉ ፈገግ ብላ
<<እኔ ምለዉ ግን ቆይ በዛዉ ጠፍቼ ቀርቼ ቢሆንስ
<ሁስኒዬ ደብዳቤ ብቻኮነዉ የተዉሽልኝ ስልክሽን ደሞ ስሞክር አይሰራም ቤት ስሄድም ሂባ የለችም ነዉ የምትለኝ
<<የዛን ቀን የሰማዉትና ያየሁት ነገር ስለከበደኝ መረጋጋቱን ስለመረጥኩ ነዉ የሄድኩት
<ሀሱ ግን እያበሳጨኝ ነዉ እያወቀ መደበቁ ያናዳል
<<ሀቢልዬ አትፍረድበት ጓደኝነታችንን ታዉቀዉ የለ ስለምነዉ ነዉ ወደ አንተ እንደምመለስ ስነግረዉ የተስማማዉ ደሞ ልጅቷን አንቀህ ልትገላት እንደነበር ሰማሁ ...
ክፍል አስራ አምስት ይቀጥላል
https://t.me/Alfaruq_islamic
https://t.me/Alfaruq_islamic
https://t.me/Alfaruq_islamic
264 viewsرب ٱشرح لي صدري ويسر لي أمري , 18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:53:37 ┏─━─━─━∞◆∞━─━─━─┓
". #ፊትና ".
✎ፀሐፊ፦ ፎዝያ ፈይሳ
┗─━─━─━∞◆∞━─━─━─
┎━─━─━─━─━─━─━─━─━┒
. በ Islamic al faruq የተዘጋጀ .
. ልብ አንጠልጣይ ታሪክ.
┖━─━─━─━─━─━─━─━─━┚
{ክፍል 13}

""ወደ አባቴ ቤት ሄድኩኝ አባቴ ቤት ስገባ ግን የማየዉን ማመን አቃተኝ ሳሎን ላይ አንዲት ሴት ተቀምጣለች ገና ከመግባሄ ሀይ ጋይስ ብላ እንደምታቀኝ ሰዉ ተነስታ አጠገቤ ደረሰችና ልታቅፈኝ እጇን ዘረጋች እኔም ይቅርታ ሀጂ ነብይ ሴት አልጨብጥም ብያት ወደ አባዬ ክፍል አመራሁ አባዬ ሁሌ የራሱ ቤታችን ዉስጥ ባለዉ የራሱ ቢሮ ነዉ ቁርሱን የሚበላዉ ግፋ ቢል እስከ ዙሁር ሰአት ይቀመጣል እናም እኔ በቀጥታ ወደ ፎቅ በመዉጣት አባዬ ጋር አንኳኩቼ ገባሁ <<አሰላም አለይኩም አቡ
<ወአሌይኩም ወሰላም የኔ ልጅ መጣህ
<<አዎ እኔ ምልህ አባቴ ሳሎን ያለችዋ ሴት እዚ ለምን መጣች ምን ትሰራለች
<አይ ልጄ ወንድምህን አሞላቀን አሳደግነዉና ይህዉ ክርስቲያን ሴት አግብቶ አሰልማለሁ እያለ ነዉ እሷ ደሞ ያዉ ስርአት ቲኒሽ ይጎላታል
<<አባዬ የልጅህ ስህተት በጣም በዛኮ እንደዉም አንተ ዝም በል እኔዉ ከቤት አባራታለሁ ብዬ ስንደረደር ወደ ታች ወረድኩና የተቀመጠችበትን ስመለከት የለችም ወደ ወንድሜ መኝታ ክፍል ስገባ የለችም <አባዬ እኔን እየተከተለ ተዉ ባክህ ተረጋግተን እናዉራበት
<<አባዬ ምንም የምናወራዉ ነገር የለም አባቴ የልጅህ ስህተት የሰዉን ሂወት አደጋ ላይ እየጣለ ነዉ ብዬ ዉጪ መናፈሻዉን ሳየዉ ቁጭ ብላ ስልክ ታወራለች ሄድኩና ይቅርታ ስምሽ ማነዉ
<ብሌን
<<አድናን ምንሽ ነዉ
<ባሌ
<<ተጋባቹንዴ
<ያዉ የቀረን ሰርግ ብቻ ነዉ እኛ ከተጣመርን ቆይተናል
<<ምን ማለት ነዉ ይሄ ቆይ ሴት አይደለሽንዴ ክብርሽን አትጠብቂም ደሞ ካለ ጋብቻ እንዴት አታፍሩም
<ዋት ምን ማለት ነዉ ይሄ እኛ ከተዋደድን አይበቃንምንዴ በዛ ላይ እንዋደዳለን ይገባሀል ብላ አፈጠጠች ባልፈልግም እጇን እየጎተትኩ ከጊቢ ላስወታት በሀይል እጎትታት ጀመር አዎ መጎተቴ ትክክል ነዉ የሂባ የዛች የሚስኪኗ እህቴ ሂወት የተበላሸዉ በሷ የተነሳ ነዉ ወንድሜን ይቺ ልጅ ባታጠመዉ ኖሮ እንደዚህ ሊጎዳት አይችልም ብቻ ከበሩ ስደርስ ሰራተኛችንን የሷን ልብስ ከአድናን ክፍል እንድታመጣ አድርጌ ከጊቢ አሶጣዋት አባቴ በኔ ዉሳኔ አልተቃወመም እሷን አሶጥቼ በሩን በሀይል ወረወርኩትና አባዬ እኔን ልታጣኝ ካልፈለክ ይቺ ልጅ እዚ እንዳትገባ የገባች ጊዜ ግን አጠገብህ አልደርስም ብዬ አጠገቡ ከመቆሜ በሩ በሀይል ተንኳኳ ዘበኛዉ ሊከፍተዉ ሲል አይ ተወዉ ብዬ በሩን ስከት ወንድሜ ነዉ
<<እሺ ጎሮምሳዉ
<ትሰማኛለህ ሚስቴን የማባረር መፍት የለህም ገባህ ይሄ የአባቴ ቤት ነዉ
<<ብቻህን መግባት መፍትህ ነዉ አለበለዚያ ግን በፍፁም ይቺን ሴት ይዘህ አትገባም ገባህ
<እንደሳ ከሆነ አንተ ወንድሜ አይደለህም ብሎ ወደቤት ገባ ከደይቃዎች ቡሀላ ልብሱን በሻንጣ ሞልቶ ወጣ አባዬ ተመለስ ቢለዉም እናንተ ቤተሰቦቼ አይደላቹሁም ብሎ ወጣ እኔም አባዬን ፈጠን ብዬ ወደ ባንክ ወሰድኩትና ቡኩን እንዲያሳግድበት ነገርኩት አባዬም አላሳፈረኝም አሳገደበት
<<አባዬ በጣም ነዉ የማመሰግነዉ አሁን እጁ ላይ ያለዉ ገንዘብ ሲያልቅ ይመጣልሀል ብዬዉ ቲኒሽ አወራንና እኔ ወደ ቤት መጓዝ ጀመርኩ።

""ሂባዬ በሩን ክፈቺ እስቲ
<እሺ እከፍታለሁ ብላ እህቴ በሩ ጋር ብዙ ቆየች እኔም የመቆየቷ ሚስጥር ስላልገባኝ ወደ በሩ ሄጄ ከዋላዋ ቆምኩና እህቴ ማነዉ የመጣዉ ብዬ እሷ ዞር እስክትል ጠብቄ የእህቴ ቦታ ቆምኩኝ የቆመችዉ በጣም ቆንጆ ሴት ነበረች ፈገግ ብዬ አሰላም አለይኩም አልኳት
<ሰላም ሁስኒያ ማለት አንቺ ነሽ
<<አዎ እኔ ነኝ እና አንቺን ማን ልበል
<ፈልጌሽ ነበር
<<እሺ ወደ ዉስጥ ትገቢ ብዬ አስገባዋት ጊቢ ገብታ በጣም አንገቷ እስኪታመም ተዟዙራ ትመለከተዉ ጀመር እናም ወደ ቤት እንድትገባ ስጋብዛት
<ኖኖኖ አልገባም ከቻልሽ እዚህ እንቀመጥና እናዉራ ብላ ዉጪ የተሰራ መቀመጫ ነበርና ጊቢ ዉስጥ ተቀምጠን ሂባ ሻይ እንድታመጣ ነግሬአት ተስተካክላ እየተቀመጠች ይገርምሻል ከሀቢል ጋር የመረጣችሁት ቦታ አሪፍ ነዉ ሰፊ ግቢም አለሽ እድለኛ ነሽ ለእንዳንቺ አይነቷ ሰራተኛ ሊያደርገዉ እንደሚችል አዉቅ ነበር ግን ታዉቂያለሽ
<<ማለት ምኑን
<በኔና በሀቢል መሀል ገብተሽ እንደሰመጥሽ
<<አልገባኝም
<ይወልሾ ሁስኒ ሀቢል የኔ የብቻዬ ነበር ነገር ግን አንቺ መተሽ ለየሽን ካላመንሽ ፎቶ ላሳይሽ ብላ በስልኳ ከሀቢል ጋር የተነሱትን ብዙ ፎቶዎችን አሳየችኝ እረ ጉዴ ብዙ ነዉ ከነ በሀራም እየተሳሳሙም የተነሱት ነበር ምንም ሳልል ስልኳን መለስኩላት
ለማንኛዉም ሙሪዳ እባላለሁ ብላኝ ስላስተናገድሽኝ አመሰግናለሁ ብላ ከጊቢዉ ለቃ ወጣች።

"""ኡፍ ዛሬ ደሞ ምን ሆነዉ ነዉ ብዬ ከመኪናዬ ወርጄ በሩን ባንኳኳ የሚከፍት የለም ግራ ገባኝ ትርፍ የጊቢም የቤትም ቁልፍ ስለነበረኝ ከፍቼ ገባሁ ወደሳሎንም ስገባ ማንም የለም ለሁስኒ ስደዉል አታነሳም እንደምንም ብዬ ወደ መኝታ ክፍል ልብስ ለመቀየር ገብቼ ቁምሳጥኑን ለመክፈት ወደ አልጋዉ ስሄድ ነጭ ወረቀት ተቀምጧል ሲመስለኝ መልእክት ያለዉ ይመስላል ስከፍተዉ__
ትሰማኛለህ አንተም ከወንድም የሚለይህ ምንም ነገር የለም እኔ የምትሻሻልና ግልፅ መስለህኝ ነበር ነገር ግን ሀቢል አንተም ልቤን ሰበርከዉ ሀቢል በቃ ከሂወቴ ዉጣ እህቴ በወንድምህ እኔ ደሞ በአንተ የተነሳ ሂወቴ ተመሰቃቀለ በቃ ተወኝና ከሙሪዳ ጋር ሂወትህን ቀጥል። የሚል አጠር ያለ ፅሁፍ ነበር ገባኝ በቃ ሄጄ ማስረዳት ስለሚኖርብኝ ብዬ በቀጥታ ወደ ሁስኒ ቤት አመራሁ ነገር ግን ቤት ሂባ ና ኡሚም አቢም አሉ ነገር ግን ሁስኒያ አልመጣችም አሉኝ ስደዉልላት ከነ ስልኳን አጠፋችዉ
በጣም ጨነቀኝ ብቻ ወደ ቤት ስሄድ ሙሪዳ በሬ ላይ ቆማ አየዋት በጣም እራሴን መቆጣጠር እየተሳነኝ መጣ ከመኪናዬ እንደምንም ወርጄ ሙሪዳ አጠገብ ሄጄ ቆምኩኝ እሷ እንደለመደችዉ ሰራሁልህ እያለች የፌዝ ሳቅ ትስቅ ጀመር ምንም ሳላወራ አንገቷን ከግንብ ጋር አጣብቄ አነኳት ልታስለቅቀኝ ብትሞክርም አልቻለችም ሰፈራችን ጭር ያለ ስለሆነ ማንም አላየኝም እኔ ግን ከሰከንድ ሰከንድ በሀይል እያነኳት መጣሁና ትንፋሿ እየተቋራረጠ በስተመጨረሻ እጄን ለማስለቀቅ መሞከሯን ትታ ፀጥ አለች.....

ክፍል አስራ አራት ይቀጥላል
https://t.me/Alfaruq_islamic
https://t.me/Alfaruq_islamic
278 viewsرب ٱشرح لي صدري ويسر لي أمري , 18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 21:16:20 ┏─━─━─━∞◆∞━─━─━─┓
". #ፊትና ".
✎ፀሐፊ፦ ፎዝያ ፈይሳ
┗─━─━─━∞◆∞━─━─━─┛
┎━─━─━─━─━─━─━─━─━┒
. በ al faruq Islamic የተዘጋጀ .
. ልብ አንጠልጣይ ታሪክ.
┖━─━─━─━─━─━─━─━─━┚
{ክፍል 12}
<<አይንህን ደግሜ ሳላጠፋዉ ከዚ ሂድ ጥፋ አንተ ወንድሜ አይደለህም ይገባሀል ብዬ እንባዬ እየመጣም ቢሆን ከፊቱ ዞር አልኩና ወደ ሂባ ክፍል ገባሁ እሷ ተኝታ ማናችንንም ማየት አልፈለገችም ፊቷን ለጊድጊዳ ሰታ ታለቅሳለች ሁስኒም የሂባን አልጋ በሁለት እጇ አጎንብሳ ይዛ ተክዛለች እኔ ምንም ማዉራት አልፈለኩም ሄጄ ሂባን ለማዉራት ስለፈለኩ ሁስኒን ለጊዜዉ እንድትወጣ አደረኩኝ ሁስኒ በኔ ትእዛዝ ምንም ሳትቃወም ወጣችና ዉጪ ተቀመጠች እኔም የሁስኒን መቀመጥ አይቼ ወደ ሂባ አልጋ ሄጄ ከተቀመጡት ሁለት ወንበሮች አንዱን ይዤ ሄድኩና ተቀመጥኩ ሂባዬ የኔ ታናሽ እህት እኔንስ ተቀይመሽኛል
<አንተ ምን አደረክና አንተን እቀየምሀለዉ
<<የጎዳሽ ወንድሜ መሆኑን ማመን እስኪከብደኝ ድረስ ነዉ ልቤ የታመመዉ
<ጥፋተኛዋ እኔዉ ነኝ እሱን ማመኔ ይጎዳኛል ብዬ አለማሰቤ የበለጠ ጥፋተኝነቴ የቱ እንደሆነ ታዉቃለህ
<<አይ አላዉቅም
<ሀቢል የበለጠ ጥፋቴ ደሞ አሁንም ድረስ እሱን አለመጥላቴ ነዉ
<<አድናንን እንደ ታላቅ ብቻም ሳይሆን እንደ አባትም ሆኜ ነበር ያሳደኩት
<አባትህስ
<<አባቴ ከሀገር ዉጪ ስለሚመላለስ ይበልጡኑ ከኔና ከኡሚ ጋር ነበር የሚያሳልፈዉ ከኛ ጋር ነበር እናቴ ስትሞት እሱ ገና ወጣትነት ላይ እየገባ የ12 ተኛ ክፍል ተማሪ ነበር እኔ ደሞ ከተመረኩኝ ስለቆየሁ የአባቴ ድርጅት ላይ ተራ ተቀጣሪ ሆኜ ነበር የምሰራዉ እናም እናታችን ስትሞት ወንድሜ ይበልጡኑ ጊዜ ከኔ ጋር ያሳልፍ ጀመር እኔም የእናቴን ሞት እንዳያስታዉስና ልቡ የማጣት ስሜት እንዳይሰማዉ በማሰብ እሱን እየተንከባከብኩኝ ግን እኔም ወደ ማይሆን ሀራም ላይ ገባሁ በዛዉ ወንድሜ እንደፈለገ መሆን ጀመረ ግን የዚህን ያህል ሴትን ልጅ ይጎዳል ብዬ አስቤ አላዉቅም ሂባዬ እኔ የእናቴን ሞት ህመሜን የረሳሁት በእህትሽ ሁስኒ ነዉ ግን እሷ ለኔ ሰበብ ሆና አክማኝ እኔ ደሞ እሷን ላሳምማት አልፈልግም ስለዚህ ከወንድሜ ጋር የነበረኝ ነገር እዚህ ላይ ያበቃል ላንቺ ብዬ ሳይሆን ለሁስኒ ብዬ ነዉ ሁስኒ የአንቺ ህመም ምን ያህል እንዳሰቃያት እኔዉ ነኝ የማዉቀዉ ብቻ ሚስቴ በኔና በኔ ዙሪያ ባሉ ሰዎች የተነሳ እንድትታመም አልፈልግም እሷ ማለት የኔ ሚስት ብቻም ሳትሆን እህቴም ናት
<ሀቢል እሱ ወንድምህ ነዉ መቼም ልትተወዉ አይገባም ምክንያቱም ዝምድናን መቁረጥ ሀራም ስለሆነ ተረዳህኝ
<<እሱስ ልክ ነሽ ግን በቃ መቅረብ አልፈልግም አሁን ሁስኒ ብቻዋን ስለሆነች ብርድም ስለሆነ ሄጄ ላምጣት ብዬ ወደ ዉዷ ሚስቴ ሄድኩኝ ሁስኒ በትካዜ ዉስጥ እንዳለች ነዉ እኔን ስታየኝ ፈገግ አለችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ተጠመጠመችብኝ
<<የኔ ባል ምንም ማዉራት አልፈልግም አሁን ወደ ቤት እንመለስ ሂባን ይዘናት ብላ ሄደን ሂባንም መዉጣት ስለምትችል ይዘናት ወጣንና ለሀሱ ደዉዬ ቤት እንዲጠብቀን አደረኩና እኔ ወደ ቤት ይዣቸዉ ሄድኩኝ ሀሱ ቀድሞን ስለደረሰ አብረን ገባንና ሂባን አስተኛናት ሀሱም አጠገቧ ቁረአን ሲቀራላት ከቆየ ቡሀላ እኔማ ሀሱ አንድ ላይ እንግዳ ማረፊያ ተኛን ሂባና ሁስኒ አንድ ላይ የኔና የባለቤቴ ማደሪያ ተኙ።

""አንተ ሀቢል ተነስ ስልክህ እየጮህ ነዉ ተነስ
<<ሀሱ ግን በቃ አርፎ መተኛት አትችልማአ ይቆረቁርሀል ብዬ የተደወለዉን ቁጥር ሳየዉ አባቴ ነበር የደወለዉ
ሄለዉ አሰላም አለይኩም አቢ
<ወአሌይኩም ወሰላም የኔ ልጅ ያዉ ሱቢሂም ስለደረሰ ነዉ የደወልኩት እናም እስቲ ወደ ረፋድ አካባቢ ወደኔ ጋር ብቅ በል
<<አንተ የት ነህ
<እኔማ ያዉ እቤት ነኝ ያለሁ
<<አቢ አልመጣም
<ለምን ልጄ
<<ልጅህ የሰራኝን ጉድ እራሱን ጠይቀዉ እዛ ቤት እሱ ካለ በፍፁም እግሬ አይረግጥም
<አይ ሀቢሌ ና እሱ ጠዋት የሆነ ቦታ ስለሚሄድ አትገናኙም
<<አቢ መምጣት አልፈልግም
<ና ብዬሀለዉ ምነዉ ልጄ እኔምኮ አባትህ ነኝ የእናትህ ሞት እየጎዳኝም ቢሆን በሰብር አንድም ቀን አንተንና ወንድምህን ላለማስከፋት ስሰራ ና ሳስደስታቹ ነበር እና የአባት ዉለታ ተረስቶ በወንድም ጥፋት አባት መቀጣት አለበት ልጄ እኔንም እየቀጣህኝ መሆኑ ነዉ ብሎ ድምፁ እንደ ማዘን ሲሆኖ እሺ በቃ መጥቼ እመለሳለሁ ብዬ ስልኩን ተሰነባብትን ዘጋሁትና ሰአቱን ተመለከትኩት ሱቢሂ አዛን ወጥቷል ተነስቼ ሀሱንም ሁስኒንም ቀሰቀስኩና ሂባ ከተሻላት ተነስታ እንድትሰግድ ተናግሬ እኔ ኡዱ አድርጌ ሱና ሰግጄ እነሱ ጨራርሰዉ እስኪመጡ በጀመአ ለመስገድ እጠባበቅ ጀመር ሁሉም ተራ በተራ መተዉ ሴቶቹ ከዋላ እኔና ሀሱ ከፊት ሆነን በሀሱ አሰጋጅነት ሰላታችንን ሰገድንና ሴቶቹ ወደ ስራ እኔ ና ሀሱ ወደ ቅረአት ተሰማራን ሴቶቹ ሲንጎዳጎዱ ይሰማል። አይደርስ የለ ቁርሱም ደርሶ በላልተን ሰአቱ እስኪረፍድ እራሴን ዘና ለማድረግ ወደ ሶሻል ሚዲያ ገባሁና ፌስቡክ ሳይ ምንም ደስ አይልም አይ ብዬ ከኦላይን ልወጣ ስል በቴሌግራም መልእክት ገባ እስቲ ማነዉ ብዬ ወደ ቴሌግራም ስገባ ሀይ የሚል መልእክት ተቀምጧል ፕሮፋይሉን ለማየት ስሞክር ኮኔክሽን እንቢ አለኝና ጥዬ ወጣሁ ና ከቆይታ ቡሀላ ተመልሼ ገባሁ የቅድሙ መልእክት ስም የለዉም .ነጥብ ብቻ ነበር ያለዉ እናም እስቲ ብዬ ወደ ታች ስወርድ ከወንድሜ ጋር የተላላኩት መልእክ አየሁትና ፕሮፋይሉን ለማየት ገባሁ ኮኔክሽን ቢያስቸግረኝም ከፈተ ግን ያየሁትን ማመን አቃተኝ አንገቷ ላይ የብር መስቀል ያደረገች ሴት ናት አብራዉ ያለችዉ የሚሆኑት ነገር ብዙም ደስ አይልም ከመጀመሪያዉ እስከ አስር የሚሆነዉ ፕሮፋይል ላይ ሳይ ከልጅቷ ጋር ከመተቃቀፍ በዘለለ ምንም የለም ግን ወደ አስራ አንደኛዉ ብሮፋይል ስሄድ ከንፈሯን እየሳማት ነዉ ቀጣዩንም ሳየዉ ከዛ የማይተናነስ ነገር ነዉ ብቻ በሁኔታዉ በሽቄ ብሎክ አደረኩትና ከኦላይን ወጣሁ ሀሱም ወደ ቢሮ ለመሄድ እየተዘገጃጀ ነበር እኔም እግረ መንገዴን ሀሱን ተከትዬ ወደ አባቴ ቤት ሄድኩኝ አባቴ ቤት ስገባ ግን የማየዉን ማመን አቃተኝ ሳሎን ላይ አንዲት ሴት ተቀምጣለች.....

ክፍል አስራ ሶስት ይቀጥላል ጆይን ይበሉ
https://t.me/Alfaruq_islamic
https://t.me/Alfaruq_islamic
297 viewsرب ٱشرح لي صدري ويسر لي أمري , 18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:28:14 ┏─━─━─━∞◆∞━─━─━─┓
". #ፊትና ".
✎ፀሐፊ፦ ፎዝያ ፈይሳ
┗─━─━─━∞◆∞━─━─━─┛
┎━─━─━─━─━─━─━─━
. በ al faruq Islamic የተዘጋጀ .
. ልብ አንጠልጣይ ታሪክ.
┖━─━─━─━─━─━─━─━─━
{ክፍል 11}

"አይ ልጄ ሀቢል ሁሉምኮ እንዳሰብነዉ ቀላል አይደለም ይቺ ልጅ ላይ የነበረን ተስፋ በጣም ትልቅም ነበር ልጄ ከመንገድ በእብደት አሰናከሉብኝ እንጂ ብላ እናቴ ምርር ብላ አለቀሰች ሀቢል አልቻለም ኡሚን ይዟት በጣም አለቀሰና እኔ ሁለቱንም አባበልኳቸዉ ሀቢልም በድጋሚ ወደ እህቴ ጋር ገባና ብዙ ቆየ እኔ ወደ ሀቢል ጋር ስሄድ እሱ ቁጭ ብሎ ቁረአን እየቀራላት እሷ ደሞ አንገቷን ደፍታ አሰየማትዉ ነበር ብቻ አልሀምዱሊላህ ዉስጤን ሲረጋጋ ይሰማኝ ጀመር ቀናቱ እየሄደ ሀቢልም ስራዉን ትቶ ወደ እኛቤት አብረን ከገባን አስራ አምስት ቀን ሆነን ሀቢል ሁሌ ከሱቢሂ እስከ እረፋድ ከመግሪብ እስከ ኢሻ ለሂባዬ ቁረአን እየቀራ እሷ እንደድሮ የምታሳየዉን ባህሪ ተወች እናም እሱ እንደ ታላቅ የሚያስፈልጋትን ሁሉ ማሟላት ጀመረና በስተመጨረሻም የስነልቦና ሀኪም ጋር ህክምናዋን እንድትከታተል አደረገ ከተጋባን አንድ ወር ከ20 ቀን ቢሆነንም ግን ሀቢል ግማሹን ቀን እኛ ቤት ነዉ ሳይሰላች በፍቅር የኖረዉ አሁን እሱም የሚፈልገዉ ነጥብ ላይ ስለደረሰ ወደ ቤታችን ተመለስን አልሀምዱሊላህ።

""ዛሬ ሀሱንም እህቴንም የሀቢልንም አባት እና የእኔ አባትና እናትንም ለእራት ጋብዘናቸዉ እኔም ባሌም ሽር ጉድ እያልን በመሀል እህቴ ስራ ይከብዳታል ብላ ስላሰበች ከሁሉም ቀድማ እቤት መጣችና የሚሰራራ መፈለግ ጀመረች ከሀቢል ጋርም በጣም እንደ ታላቅና ታናሽ እየተቀራረቡ ስለነበር ደስተኞች ሆነዉ ከኔ ጋር እየተፎጋገሩ ስራ እየሰሩ ነዉ ደስ የሚለዉ ምሽት ደረሰና ሀሱ መጣ ያዉ ሀሱ እህቴን የተወሰነ ተመላልሶ እየጠየቃት ስለነበር አዲስ ሰዉ አልሆነባትም አልሆነችበትም ገብቶ እየተጫወተ ግን ሀቢል የተወሰነ እኔን ስራ ሊያግዘኝ ተነሳ።

""አልሀምዱሊላህ ሂወት ደስ ከማለቷ በዘለለ የኔ ሚስትም እህቷም ደስታቸዉ ተመልሷል በነገራችን ላይ የሂባን ጉዳይ አረሳሁትም ልጁን በሆነ መንገድ እስከማገኘዉ በጣም ነዉ የጓጓሁት ምክንያቱም ሁስኒ ከልጁ ዉጪ ሰዉን ማፍቀር እንደማትችል እራሷን አሳምናዋለች ብቻ አለህ ገር ቢያረገዉ ሂባን ከሀሱ ጋር ቢጋቡ ብዬ አስቤ ነበር ብቻ አልሀምዱሊላህ።
<<ሀቢልዬ እንዴ ቆይ ጁስ መፍጨት የዚህን ያህል ያቆያልንዴ
<የኔ ሚስት መጣሁ ያዉ ታዉቂያለሽ እንዳንቺ ጣፋጭ እስኪሆን ድረስ ለመስራት ነበር እናም መጣሁ ብያት ወደ ስራዬ ተመለስኩ በመሀል ሀሱ ለነቆራ አጠገቤ መጣ
<<ይገርማል የሆነ ሰዉ ሰራተኛ ለሚስቱ ቅጠር ሲባል ለካ እምቢ ያለዉ የራሱን ሞያ ተማምኖ ነዉ ለካ
<ሀሱ እሱ ነቆራህን ቡሀላ እንደርስበታለን ይልቁኑስ አንተ ስለራስህ ሂወት ምን እያሰብክ ነዉ
<<ወንድሜ ያዉ ምን አስባለዉ ብለህ ነዉ ብሎ ፊቴን ወደ ፍሪጅ ሳዞር እሱ ለሚስቴ ያስተካከልኩትን ጁስ ሊጠጣ መቅዳት ጀመረ
<በቃ የሆድህ ነገር አይሆንልህማአ
<<አንተ ምን አስበህልኝ ነዉ
<እኔማ ሂባን ብታገባት ብዬ ነበር ብዬ ስለሷ ብዙ ህመሟንና ጉዳቷን ጨምሬ ነገርኩት ስለ አስተሳሰቧም ጥሩነት ነገርኩት
<<ያሰብከዉ ሀሳብ ጥሩ ነበር ግን አሁን ጁሱንም ስለጨረስኩ ወደ ሳሎን ሄጃለዉ ብሎኝ ወጣ እኔም ከነበርኩበት ሀሳብ ስባንን ሀሱ የጠጣብኝ ለሚስቴ ብቻ ያዘጋጀሁትን ሁሉንም ነበር በቃ ሀሱ እንደዚህ ነዉ በተለይ ጁስ ካየ በበርሜልም ተሞልቶ ቢሰጠዉ ሚጨርሰዉ ነዉ የሚመስለኝ ይቺማ ምን አላት ሁለት ብርጭቆ ብትሆን ነዉ እና ለካ ጨርሻለሁ ብሎኝ የሄደዉ ለዚ ነዉ ብዬ በድጋሚ ጁስ ለማዘጋጀት ደፋ ቀና ስል ሚስቴ መጣችና እንዴ የኔ ባል ጁሱ የት ሄደ አለችኝ ግራ ተጋብቼ ስርበተበት የመኪና ክላሲካል ሰማን እሷም ቡሀላ ታወጣታለህ ብላኝ ፈገግ ብላ ወደ ሳሎን አመራች ከቤት ስወጣ የመጡት አባቴና ወንድሜ ናቸዉ ማሻአላህ ብዬ ዲንገተኛ ሰርፕራይዝ ስለነበር ወደ ጋቢና ተጠግቼ ወንድሜን አቅፌዉ ሰላም አልኩት አባቴንም ሰላም ለማት ስሄድ
~የኔ ልጅ ያዉ መምጣቴን እንዳትነግረዉ ብሎኝ ነዉ ዝም ያልኩት
<<እረ አባዬ አታስብ እሱንማ እንደሚያረገዉ ጠንቅቄ አዉቃለሁ
<ወንድሜ አባቴን ተወዉ ወደ ቤት ይግባና እኔና አንተ እንደ ልጅነታችን አየር ወስደን እንግባ
<<አንተ ሚስቴን ለማየት አለመጓጓትህ ግን ይገርማል የእዉነት
<ያዉ ታዉቃለህ እኔ ነገሮች ላይ ቲኒሽ
<<አዉቃለሁ እና አንተ እንዴት ነህ ደሞ ሚስቴን በቶሎ ተዋወቃት
<እረ እተዋወቃለሁ ግን አዲስ ነገር ነበር እሱን አዉርቼህ ብንገባ ይሻላል ብዬኾ ነዉ ብለን እያወራን የጊቢዉ በር ተንኳኳ ማነወ ብሎ ዘበኛዉ በሩን ሲከፍተዉ የነበሩት የሁስኒ እናትና አባት ናቸዉ።
ሁስኒ ከቤት ሁቢ እያለች ወጣችና ና ግባ እንጂ አለችኝ ወንድሜን በደንብ አላየችዉም መነፅር አድርጎ በዛ ላይ ምሽት ስለነበር ሹራቡ እስከ አፉ ስለሸፈነዉ ፈገግ ብላ አሰላም አለይክ ብላን አለፈች ወንድሜ ግን እንዴ አለ ምነዉ ስለ ምንም ብሎኝ ወደ ቤት ለመግባት በሩ ጋር ቲኒሽ ቆመ እኔ የሁስኒን እናትና አባትን ሰላም ብዬ ወደ ቤት ይዣቸዉ እየገባሁ ወንድሜ አሁንም ቋሟል ሁስኒ እረ ግባ ደሞ ማነዉ አላስተዋወከኝምኮ ብላ ወደ ወንድሜ ዞረች እሱም ምንም ሳያወራ ገባ የሱ ሁኔታ ቢያስገርመኝም መቼስ ከኔ ቀድሞ ያዉቃታል ማለት ከባድ ነዉ።
ሁላችንም ገብተን ቲኒሽ ከተጨዋወትን ቡሀላ ወደ እራት ጠረፔዛዉ ሄደን ቁጭ አልን በመስመር እኔ ከአባቴ አጠገብ ከኔ ቀጥሎ ሁስኒ ከሁስኒ ቀጥሎ እህቷ ሂባ ከእህቷ ቀጥሎ ደሞ ሀሱና እናቷ አባቷ በኔ ፊት ለፊት ወይም በዙሪያ የተቀመጠዉ ወንድሜ ነበር እስካሁን እያወሩ እራት ቀርቦ ስለነበር ወንድሜ ቁራቡን ዝቅ አድርጎ መነፅሩን አወለቀ በዚህን ጊዜ ሂባ ምን ብላ ተነሳችና አይሆን እያለች ወንበሯን ለቃ ወደ ሁዋአላ መሸሽ ጀመረች ሁስኒም አንተ ብላ ወንድሜ ላይ አፈጠጠች በዚ መሀል ሂባ እራሷን ስታ ወደቀች ሀሱ ሂባን ተሸክሞ ሶፋ ላይ አደረጋትና ዉሀ ቢያረግባት ልትነቃ አልቻለችም በጣም ስትቆይ ሁስኒም እያለቀሰች ወደ ሆስፒታል ወሰድናትና የሷን ድህንነት መጠባበቅ ጀመርን ሂባ ልትነቃ አልቻለችም እሚገርመዉ ወንድሜም አብሮን አለ ግራ ገብቶኝ ታዉቃታለህ ስለ አዎ ግን እኔ የዚህን ያህል የሚያደርስ ትዉዉቅ የለንም ብሎን እሱ ጥጉን ይዞ ተቀመጠ የሁስኒ እናትና አባትን ሁስኒ ሀሱ እንዲሸኛቸዉ አድርጋ የኔም አባት እስኪወጣ ጠብቃ ወደኔ መጣችና ከወንድሜ አጠገብ ተቀመጠች
<ትሰማኛለህ ማን አባህ ስለሆንክ ነዉ ተመልሰህ የመጣህዉ ብላ ሁስኒ ወንድሜ ላይ አፈጠጠችበት እኔ የሚሆነዉን መከታተል ስጀምር ዶክተሩ ወቶ የሂባ ቤተሰቦች ብሎ ሲጣራ እሱን ትታዉ ወደ ሂባ ጋእ ገብታ ቲኒሽ ቆየችና ወጣች እናም ወንድሜን አነቀችዉ እረ እኔ ብገላግላትም ላስለቅቃት አልቻልኩም ወንድሜ ጥርሱ እስኪረግፍ ቀጥቅጣዉ በመከራ ለቀቀችዉ እኔ ሁኔታዉ ቢያወዛግበኝም ግን ማንን መጠየቅ እንዳለብኝ ግራ ተጋብቼ ዝም አልኩና ወደ ሁስኒ ሄድኩኝ ሁስኒ ምንድ ነዉ ብዬ ጠየኳት እሷም አድናን አድናን እሱ ነዉ
<አዎ ነዉ ግን ምን ሆነ ምን አረገ አልኳት

https://t.me/Alfaruq_islamic
335 viewsرب ٱشرح لي صدري ويسر لي أمري , 18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ