Get Mystery Box with random crypto!

ለሞተ ሰው ብለን ቁርአን ብንቀራ አጅሩ ይደርሰዋልን የዚህ ጥያቄ መልስ ኢብኑ ባዝ አላህ ይዘ | የነብዩ ☪ሠ,ዐ,ወ☪ ሀዲሶች

ለሞተ ሰው ብለን ቁርአን ብንቀራ አጅሩ ይደርሰዋልን

የዚህ ጥያቄ መልስ ኢብኑ ባዝ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ያብራሩታል።

ይህ ተግባር መሰረት የለውም። ለሟች ዱአ ቢደረግለት ይደርሰዋል። ለሱ ተብሎ ቁርአን መቅራት ግን መሰረት የለውም። የሚደነገግ ተግባርም አይደለም። አንድ ሰው ለሟች ሳይሆን ለራሱ አጅር ማግኘትን አስቦ መቅራት አለበት።»

ለሙታኖች አላህ እንዲያዝንላቸውና እንዲምራቸው ዱአ ይደረግላቸዋል። ሰደቃም ይሰጥላቸዋል። ሀጅም ይደረግላቸዋል። እነዚህ ይደርሳቸዋል። አልፎም ይጠቅማቸዋል።

ነገር ግን ለሙታን ተብሎ ቁርአን መቅራትና ሶላት መስገድ ግን መሰረት የሌለው ተግባር ነው። ቢፈፀም ራሱ ለነሱ አይደርሳቸውም። ምክንያቱም ለሞተ ሰው ቁርአን እንደሚቀራለት የሚያሳይ አንድም መረጃ የለምና።

አምልኮቶች በቁርአንና በሀዲስ የተገደቡ ናቸው። የአላህ መልእክተኛ በሀዲሳቸው (የኛን ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ,ስራው, ተመላሽ ነው) ብለዋል። ከነብዩም ሆነ ከአንድም ሶሀባ ለሞተ ሰው ቁርአን ይቀሩ ነበረ የሚል ነገር አልፀደቀም።

ለሞተ ሰው ይበልጥ በላጭና የሚጠቅመው ነገር ምንድ ነው? ተብለው ተጠይቀው «ዱአ ማድረግና ሰደቃ መስጠት ነው። ይህ እጅግ በጣም ይጠቅመዋል» ብለው መልሰዋል።
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን
JOIN

@Adnan567mh