ወዳጄ በሽምግልና ዘመንህን በደስታ ማሳለፍ የምትፈልግ ከሆነ የወጣትነት ዘመንህ ለክርስቶስ አቅርብ።በወጣትነት የተሰበሰበ በሽምግልና የድካም ዘመን ያሉትን የሚመግብና የሚያጽናና ነው። የሞትህ ጊዜ አይታወቅምና በወጣትነትህ ጊዜ በጽናት ሁነህ ድከም፣በንቃትም እሩጥ ።በእጃቸው እሳት ይዘው የእግዚአብሔርን ቤተመቅደስ በውስጡ ባለው እሳት ለማቃጠል የሚጥሩ አደገኛ ጠላቶች አሉብህ።የምትሮጥ ከሆነ ሎጥን እንጂ ሚስቱን ባለመምሰል ሽሽ። ዲን አክሊል ዘሰዋስው @zsewasw 417 viewsሰዋስው, 08:59