Get Mystery Box with random crypto!

ዘሀገረ~ኢትዮጵያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zhagerethiopia — ዘሀገረ~ኢትዮጵያ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zhagerethiopia — ዘሀገረ~ኢትዮጵያ
የሰርጥ አድራሻ: @zhagerethiopia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 793
የሰርጥ መግለጫ

👉🏿ወቅታዊ እና ፈጣን መረጃዎች፣
👉🏿የመዝናኛ እና ስፖርታዊ ዜናዎች፣
👉🏿የምሁራን እይታዎች እና መፅሀፍቶች፣
👉🏿ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ይዳሰሳሉ!!
ለማንኛውም መረጃ @ZHagerEthiopiabot

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-02-20 08:09:54
የታላቁ ህዳሴ ግድብ እውነታዎች......

ግድቡ 5,150 ሜ.ዋ ሀይል የማመንጨት ሀይል አለው

13 የሀይል ማመንጫ ዩኒቶች (ተርባይኖች) የተገጠሙለት ነው

እያንዳንዱ ተርባይን 375 ሜ.ዋ በላይ የማመንጨት አቅም አለው

ግድቡ 145 ሜትር ወደ ላይ ይረዝማል፤ ወደ ጎን ደግሞ 1.8 ኪ.ሜ የሚሸፍን ሆኖ ነው የተገነባው

ከዋናው ግድቡ ሞልቶ የሚወጣው ውሃ ሳድል ግድብ (ኮርቻ ግድብ) ውስጥ ይከማቻል

ኮርቻ ግድብ 50 ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን ወደ ጎን 5.2 ኪ.ሜ የሚሸፍን ነው

በአጠቃላይ የህዳሴ ግድብ 74 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ የመያዝ አቅም ያለው ግድብ ነው።

አጠቃላይ እስካሁን ባለው መረጃ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ 16.2 ቢሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል

ግድቡ አሁን ያለበት ደረጃ 1ኛ እና 2ኛ ዙር የውሃ ሙሌት ተጠናቋል

በነገው እለት አንዱ ተርባይን ሀይል የሚያመነጭ ይሆናል

አጠቃላይ የግድቡ ግንባታ 83.9% ተጠናቋል

ግድቡ ለቱሪዝም፣ ለአሳ ሀብት ለኤሌክትሪክ ሀይል ፍጆታ ጠቀሜታዎች አሉት

ከግድቡ ግንባታ ጋር ተያይዞ 246 ኪ.ሜ የሚሸፍን አርቴፊሻል ሀይቅ ይፈጠራል።

@ZHagerEthiopia @ZHagerEthiopiaBOT
656 viewsedited  05:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-17 13:01:35
ጠ/ ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካን ቡድናቸው በሦስተኛው የቱርክ አፍሪካ አጋርነት ጉባኤ ለመሳተፍ ቱርክ፣ ኢስታንቡል ገብተዋል።

@ZHagerEthiopia @ZHagerEthiopiaBOT
1.2K viewsedited  10:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-16 06:40:17
#መልካም_ዜና

የኢትዮጵያን አሜሪካን ሲቪክ ካውንስል ትላንት ከከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር ባደረገው ስብሰባ መሰረት፣ ኢትዮጵያን በጅኖሳይድ ለመጠየቅ በሴኔት ቢሮ የታሰበው #HR_4350 ውስጥ #አንቀፅ_6464_ከረቂቅ Determination of potential Genocide or crimes Against Humanity የሚለው ሙሉ በሙሉ ህጉ መሰረዙን ይፋ አድርጎል።

ይሄ ስኬት በድል እንዲጠናቀቅ ሌት ተቀን የሰራችሁ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳችሁ። ከተባበርን ከለፋን፣ የትብብራችን ሀይልና የላባችንን ውጤት ማንም አይወስድብንም !

Via: suleman abdela
@ZHagerEthiopia @ZHagerEthiopiaBOT
1.3K viewsedited  03:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-14 21:14:45
በትግራይ፣ አማራና አፋር ክልሎች የተፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመመርመር ዶ/ር ታደሰ ካሳ ተሾሙ!

በትግራይ፣ አማራና አፋር ክልሎች የተፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመመርመር፣ ጥፋተኞችን በህግ ተጠያቂ ለማድረግና ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋም የተመሰረተው የሚኒስትሮች ግብረ-ሃይል ዶ/ር ታደሰ ካሳን የግብረ-ሃይሉ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አድርጎ መሾሙን አሳውቋል፡፡

@ZHagerEthiopia @ZHagerEthiopiaBOT
889 viewsedited  18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-12 20:15:56
የራስ ተፈሪ ማህበረሰብ #nomore ሰልፍ በጀማይካ
~~~~~~~~~~~~

ጀማይካውያን የራስ ተፈሪ ማህበረብ አባላት በኪንግስተን #kingston ከተማ በኢትዮጵያ ላይ የሚካሄደውን የምዕራብ ሃገራት ጫና እና የሚዲያ ዘመቻ የሚቃወም ሰልፍ አካሂደዋል። በዋና ከተማዋ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ደጅ ላይ የባይደን አስተዳደር አቋምን የሚተች መፈክር አሰምተዋል።

እንደ ኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር መረጃ ሰልፈኞቹ የአሜሪካ መንግስት የኢትዮጵያን ሉዐላዊነት እንዲያከብር፣ በውስጥ ጉዳይ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም እና ሚዛናዊ እንዲሆን ጠይቀዋል።
#nomore
#GreatEthiopianHomecoming

ሰላም ሙሉጌታ
@ZHagerEthiopia @ZHagerEthiopiaBOT
813 viewsedited  17:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-11 21:53:44
"የኢትዮጵያ ሰላም ተከብሮ ሕዝቡ በሰላም ወጥቶ እስኪገባ ድረስ ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነን "

ሜጀር ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
@ZHagerEthiopia @ZHagerEthiopiaBOT
622 views18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-11 21:37:17
ኦሚክሮን የተሰኘው ልውጡ የኮሮና ተህዋሲ በታላቋ ብሪታንያ በፍጥነት እየተዛመተ መሆኑ ተገለፀ።

በተለይ በለንደን ከተማ በተህዋሲው ከተያዙ ሰዎች 30 በመቶው ላይ አዲሱ ልውጥ ተህዋሲ ሊረጋገጥ መቻሉን አንድ ባለስልጣን ገልጸዋል። እንደ ጤና ባለስልጣናት ገለጻ በታላቋ ብሪታንያ በታህሳስ ወር አጋማሽ ላይ ኦሚክሮን ዋነኛው የኮሮና ተህዋሲ ሊሆን ይችላል።

የስኮትላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮላ ስተርጅን ብሪታኒያ ውስጥ ከሚከሰት « የኮሮና ማዕበል» ሕዝቡ እንዲጠነቀቅ አሳስበዋል። አርብ ዕለት በአስራ አንድ ወራት ውስጥ ከፍተኛ የተባለው ቁጥር ተመዝግቧል። በዚህም መሰረት በ24 ሰዓታት ውስጥ 58,194 አዲስ ሰዎች በተህዋሲው ተይዘዋል።

@ZHagerEthiopia @ZHagerEthiopiaBOT
560 views18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-11 19:38:00
ሳሙኤል ኢቶ የካሜሩን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመርጧል።(FECAFOOT)

@ZHagerEthiopia @ZHagerEthiopiaBOT
487 viewsedited  16:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-11 19:14:26 ሰበር ዜና!!

የወልድያ መቀሌ ጎዳና በኢትዮጵያ ጥምር ጦር መቆረጡ ተገለፀ!


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሚመሩት የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት፣ በአሸባሪው ወራሪ ላይ በሰነዘሩት ክንደ ብርቱ ማጥቃት፣ በምሥራቅ ግንባር ስትራቴጂያዊ የሆኑትንና ወራሪው በፍጻሜ ዋዜማ ላይ መሆኑን የሚያሳዩትን የዞብል ሠንሠለታማ ተራሮችን ጨምሮ ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የአርጆ፣ ፎኪሳ እና ቦረን ከተሞችን ተቆጣጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ የጉራ ወርቄ አካባቢዎችን በመቆጣጠር የወልድያ መቀሌ ዋናውን አውራ ጎዳና በመቁረጥ ጠላት መውጫ አጥቶ ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ ግንባር የድሬ ሮቃና የሶዶማ ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ከተሞችና ተራሮች በመቆጣጠር ጥምር ጦሩ ወደ ሐራ ከተማ እየገሠገሠ ይገኛል፡፡

በውጫሌ ግንባር ደግሞ የአምባሰል ከፍተኛ ሠንሠለታማ ተራሮችን ጨምሮ የሮቢትና የጎልቦን፣ በወረባቦ ወረዳ የሚሌ ኮትቻን፣ በሐብሩ ወረዳ የኮልቦን፣ የመርካታና የፋጂን አካባቢዎችን በመቆጣጣር ወደ መርሳ ከተማ እየገሠገሠ ነው፡፡

በእነዚህ ግንባሮች በተደረገው ኦፐሬሽን በአሸባሪው የጠላት ኃይል ላይ በተሠነዘረበት ማጥቃት ጠላት ሙት፣ ቁስለኛና ምርኮኛ ሆኗል፡፡የወገን የመካናይዝድ ኃይልና ንሥሮቹ የአየር ኃይሉ በጥምረት ባካሄዱት ኦፐሬሽን የጠላት ኃይል ምንም ዓይነት ተሸከርካሪ እና ከባድ መሣሪያዎችን ይዞ እንዳይንቀሳቀስ ስላደረጉት፣ ጠላት በየአቅጣጫው ጥሎ ለመፈርጥጥ ተገድዷል፡፡

[የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት]
@ZHagerEthiopia @ZHagerEthiopiaBOT
465 viewsedited  16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-11 14:15:14
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ሐሮ ሊሙ ወረዳ 19 ሰዎች በኦነግ ሸኔ ተገደሉ

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ሐሮ ሊሙ ወረዳ፣ 19 ንጹኃን ሰዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት በተፈረጀው ኦነግ ሸኔ መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ገለጹ።

የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በሠነዘሩት ጥቃት 10 ንጹኃን ዜጎች መገደላቸውንና 20 የቀን ሠራተኞች መታገታቸውን ነው።

10ሩ ሰዎች ከመገደላቸው በፊት፣ ዘጠኝ ንጹኃን ዜጎች እንደተገደሉና 12 ሰዎች እንደታገቱ የተመላከተ ሲሆን፣ በሳለፍነው ሳምንት በአጠቃላይ 19 ንጹኃን ዜጎች መገደላቸውንና 32 ሰዎች መታገታቸውን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። ሰዎቹ የተገደሉት በሊሙ ወረዳ መንደር ስደስት እና መንደር ሰባት ተብለው በሚጠሩ አካባቢዎች ነው ተብሏል።

#ዳጉ_ጆርናል
@ZHagerEthiopia @ZHagerEthiopiaBOT
431 viewsedited  11:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ