2022-11-02 23:54:53
ዛሬ የተፈረመው ስምምነት ምን ዝርዝር ጉዳዮችን ይዟል?
(ማምሻውን ካገኘሁት ባለ 10 ገፅ ዶክመንት ተቀንጭቦ የተወሰደ)
The Permanent Cessation of Hostilities:
- ሁሉም አካላት አስቸኳይ የተቃርኖ አካሄዶችን እና ውጊያዎችን እንዲያቆሙ (ከውጭ ሀይሎች ጋር ማበር፣ የአየር ጥቃቶችን መፈፀም፣ ፈንጂዎችን መትከል፣ ድንገተኛ ጥቃቶችን መፈፀም ወዘተ እንዲያቆሙ)
- ይህ አካሄድ በትግራይ ክልል ህገመንግስታዊ ስርአት እንዲመለስ እና የፖለቲካ ውይይት እንዲጀመር እንዲያስችል
- የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊትን ጨምሮ የፌደራል ስልጣን ወደ መቀሌ ከተማ እንዲመለስ እና አስፈላጊው ህዝባዊ አገልግሎት እንዲቀጥል ማስቻል
Disarmament, Demobilization and Reintegration:
- ኢትዮጵያ አንድ መከላከያ ሰራዊት ብቻ እንዳላት ግንዛቤ ተወስዶ ለህወሀት ታጣቂዎች ትጥቅ ፍቺ፣ ብተና እና መልሶ ማቋቋም (DDR) በህገ-መንግስቱ መሰረት እንዲከናወን
- ስምምነቱ በተፈፀመ በ24 ሰአት ውስጥ በሁለቱም ወታደራዊ ኮማንደሮች መሀል ግንኙነት እንዲፈጠር፣ በ5 ቀናት ውስጥ ደግሞ ውይይት እንዲያደርጉ
- የትጥቅ አፈታቱ ሂደት ለከባድ መሳርያዎች ቅድሚያ ተሰጥቶት እንዲከናወን፣ ሂደቱም ኮማንደሮቹ ከተገናኙ በሗላ በ10 ቀን እንዲጠናቀቅ፣ ትንንሽ መሳርያዎችን ጨምሮ ሁሉም ትጥቅ አፈታት በ30 ቀን እንዲጠናቀቅ
- የትጥቅ አፈታት ሂደቱ በትግራይ ክልል ያለውን የህግ እና ፀጥታ ሁኔታ ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲከናወን
TPLF Shall:
- ህወሀት የፌደራል መንግስቱን ስልጣን እንዲያከብር፣ የፌደራል ንብረቶችን፣ ተቋማትን እና አለም አቀፍ ድንበር እንዲቆጣጠር ማስቻል
- ህወሀት በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የሚገኙ ተፃራሪ ቡድኖችን መደገፍ እንዲያቆም
- ፀረ-ህገ መንግስታዊ የስርዐት ለውጥ እንዲመጣ ከማድረግ ጥረት እንዲቆጠብ... ወዘተ
The Government of the FDRE Shall:
- መንግስት የህወሀት ተፋላሚዎች ላይ ያተኮረ ወታደራዊ ጥቃት እንዲያቆም
- በስምምነቱ መሰረት ትግራይ ክልል ውስጥ አስፈላጊ የህዝብ አገልግሎቶች እንዲጀምሩ ማስቻል
- ህወሀት የተጣለበት የሽብርተኝነት ስያሜ እንዲነሳለት ማስቻል... ወዘተ
Restoration of Federal Authority in the Tigray Region:
- የፌደራል ስልጣን በትግራይ ክልል እንዲቀጥል (የፌደራል ተቋማትን መቆጣጠር ጨምሮ)፣
- የፌደራል መንግስት ደግሞ የትግራይ ክልል በፌደራል መንግስት ተቋማት እንዲወከል ማስቻል አለበት (ህዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ጨምሮ)
Transitional Measures:
- የምርጫ ቦርድ የአካባቢ እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚደረግ ምርጫ እስከሚከናወን አካታች የሆነ ግዜያዊ አስተዳደር በክልሉ እንዲኖር ማስቻል
- የሽብርተኝነት ስያሜው በተነሳ በሳምንቱ ሁለቱ አካላት የፖለቲካ ውይይት እንዲጀምሩ እና ለፖለቲካ ልዩነታቸውን መፍትሄ እንዲያበጁ
- ሁለቱም አካላት የአካባቢ ይገባኛል ጥያቄዎችን በኢፌዴሪ ህገመንግስት መሰረት እልባት እንዲሰጡ።
መልካም ምሽት።
2.0K views20:54