ጉርባዮ! ቁጡሪ ሂንቤክቱይ?
<< .... 50 ቢሊየን ችግኝ እየተከልን ነው! በቀላሉ እያንዳንዱን በ1 ዶላር እንኳ ብናሰላው 50 ቢሊየን ዶላር ነው! >> ጠሚ
- አጠቃላይ የኢትዮጵያ የቆዳ ስፋት 1,104,300 km² ነው።
የአለምን የደን ሽፋን 50 በመቶ የሚሸፍነው የአማዞን ጥቅጥቅ ዝናባማ ደን ፣ ስፋቱ ከ6 ሚሊየን km² በላይ ነው። ያ ማለት ይህ ደን ብቻውን ኢትዮጵያን 6 ጊዜ ደምረን ማለት ነው። ከትንሽ ወደትልቅ ቆጥረን የአሜሪካን 48 ስቴቶች ያክላል። ወይም ደግሞ እንግሊዝና አየርላንድን በአንድ ላይ ጨፍልቀን እንኳ በ17 ጊዜ ይበልጣቸዋል። በሌላ ስሌት በአፍሪካ ትልቁ ደን የኮንጎ ባሲን ፣ የኢንዶኔዥያ ደን ተደምሮ እንኳ ከአጠገቡ አይደርሱበትም።
ታዲያ በዚህ የአማዞን ደን የሚገኙት 390 - 400 ቢሊየን የሚገመቱ ዛፎች ሲሆኑ ፣ ወደ16 ሺህ አይነት የዛፍ ዝርያዎችም አሉ!
ታዲያ! ይህን ሁሉ ችግኝ ድፍን ኢትዮጵያ ላይ ተክለን ፣ ህዝቡን ያለቤት ጫካ ውስጥና በዋሻ እንዲኖር ከምንፈርድበት ፣ በ50 ቢሊየን ዶላሩ ከአማዞን ጥቅጥቅ ጫካ ትንሽ ገመስ አድርገን ለምን አንገዛም?
ባሻዬ! አለም ባንክ ግን << 2 ቢሊየን ዶላር አላበድርም! >> ብሎ ገግሞ ቀረ አይደል?
ሠፊው ህዝብ እሱው ይሁንህ!