ቱጃሩ አላሙህዲንን ደብዛቸውን አጥፍቶ ሀብታቸውን እየቀረጠፈ ያለው ጅብ ማን ነው? ታዋቂው ቢሊየነር ፣ በአንድ ወቅት በፎርብስ መፅሄት ከአፍሪካውያን ቢሊየነሮች ከቁንጮዎቹ ተርታ ተቀምጠው የነበሩት ፣ በአለም ላይ ከ80 በላይ ኩባንያ በኢትዮጵያ ደግሞ ከ40 በላይ ኩባንያዎች የነበሯቸው ፣ በአደባባይ ኢህአዲግ ነኝ! ብለው የፖለቲካ አቋማቸውንና የስርአቱ አጋርነታቸውን በመግለፅ የሚታወቁት ብሎም በበጎ አድራጎታቸውም የሚወሱት ፤ ሼህ ሙሐመድ አላሙዲን በሳኡዲ አረቢያ ለእስር ከተዳረጉ ጀምሮ ደብዛቸው መጥፋቱ ይታወቃል። ለውጡ እያሉ ከሚጠሩት የክፉ ዘመን ጅማሮ ላይ ጠ/ሚ አብይ ወደሳዑዲ ተጉዞ በመመለስ > ብሎ በብሔራዊ ሚዲያ ተናግሮም ነበር። ቱጃሩ ግን ጠሚው ይህን ቃል ከተናገሩ በኃላ እንኳ ጭራሽ ከሳኡዲ ንቅንቅ እንዳይሉ ካቴናው ጠብቆባቸው በቁም እስር ላይ ይገኛሉ። ከሀብት ማማ ተፈጥፍጠው ፣ ስማቸው የማይነሳ ፣ ታሪካቸው የማይወሳ ሆኖ ፣ ድርጅቶቻቸው ሁሉ ተዘርፈውና ተመናምነው ባለቤቱ እንደሞተበት ማሳ የአልፎ ሂያጁ ሁሉ መጫወቻ ሆነው ቀርተዋል። ታዲያ! ከዚህ ለምንና እንዴት ? ብለን ጠይቀን ከማናውቀው የቱጃሩ መሰወርና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ያለውን እውነታ ፥ ኢትዮ-360ዎች ትናንት > በሚል ርዕስ ባሰናዱት ፕሮግራም ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው አቅርበውታል። ይህን አስገራሚው የቂቤው ክህደት የተተነተነበት ፕሮግራም ፣ ከስር ያለውን ሊንክ ተጭነው ይከታተሉት! https://www.youtube.com/live/PdzLIGMJbog?feature=share ዘንዶው ፍፁም አይራራም! 5.4K views17:00