Get Mystery Box with random crypto!

አቤት ውርደት…! '…የእኛው ጉድ ወሬ አማረለኝ ብሎ እንዲህ ይለዋል። እዚ በእነ አገኘሁ ተሻገር | ዘሪሁን ገሠሠ

አቤት ውርደት…!

"…የእኛው ጉድ ወሬ አማረለኝ ብሎ እንዲህ ይለዋል። እዚ በእነ አገኘሁ ተሻገር ላይ መንበጫበጭ በጌታቸው ረዳ ላይ ማላገጥ ለምዶ እኮ ነው። አዲሱ የዓለም ባንክ መሪ ዕድለኛ ነህ፣ የሚታይ ሥራ ለውጥ ሳታመጣ ቱ ምን አለ በለኝ፣ ጌታ ምስክሬ ነው 2 ዓመት በቦታው ላይ አትቆይም ዓይነት ነገር ያለው መሰለኝ ። እኔ ራሴ እኮ እንግሊዝኛ ያለመማሬ እንደጎዳኝ አሁን አሁን ነው በደንብ የገባኝ። 

"…የዓለም ባንኩም መሪ ሲመል ምን ቢለው ጥሩ ነው። "የፈጣሪ ያለህ እኔ እኮ የተመረጥኩት ለ 5 ዓመታት ነው። አባቴ ምን እንዳወራህ አልገባኝም። ነገር ግን አንድ የገባኝ ቁም ነገር ይህ ንግግርህ ስላንተ ማንነት ብዙ ነገር ይነግረኛል ወይም (በሾርኔ ኢትዮጵያውያኖች በየቀኑ በአንተ የተነሣ ዋይ ዋይ የሚሉት በምን ዓይነት መሪ እየተመሩ እንደሆነ ነው አሁን የገባኝ) በልቡም ሐበሾች ሆይ ጭንቀታችሁን አሁን ገና ነው ተረዳሁት፣ ያ በጀርመን ስደተኛው ሰውዬ ዘመድኩን ዘመዴ የምትሉት "ይሄ የ7ተኛ ጨ ሰው ነው፣ ዱፍትርናውም የቁጩ ነው ዓይነት መልስ ነው የሰጠው)

"…ይሄን አረመኔ ሰው መሳይ በሸንጎ፣ በየሄደበት፣ በየደረሰበት፣ አፉን በከፈተበት ሁሉ የንፁሐኑ ደም እየተከተለው ያዋርደው ብለን የረገምነው እርግማን አሁን በግልጽ እየሠራ መጥቷል። አሳማ ሊፒስቲክ ብትቀባ አሳማነቷ እኮ አይቀየርም። አይለወጥም። መሃይምነትን ሱፍ መልበስ ሊቅ አያደርገውም።

"…You is my president ገና ከዚህ በላይ ትዋረዳታለህ። መሳቂያ መሳለቂያም ትሆናታለህ። ኢትዮጵያ ግን አንተ መቃብር ላይ ሰንደቋን ተክላ ትነሣለች። አይ ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ምን ብለው ቢረግሙን ይሆን እንዲህ ዓይነት ሼምለስ ልቡሰ ሥጋ ጋኔል ላይ የጣለን…?

"…ምንአለ ዝም ቢል…?

@ዘመድኩን በቀለ