የጉድ ሀገር ገንፎ እያደር ይፋጃል! > USAID በሚሊዮን ለሚቆጠሩ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለሚሹ ኢትዮጵያውያን የሚያደርገውን የምግብ እርዳታ ፣ በመንግስት ከፍተኛ ሌብነትና የዘረፋ እቅድ ምክንያት ለጊዜው ሙሉ በሙሉ ማቋረጡን ገልጿል! የዩናይትድ ስቴትስ አለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅት (USAID) ዛሬ ይፋ ባደረገው መግለጫው ፣ ከመንግሥት ሾልከው በወጡ ሰነዶች ፣ ከአለምአቀፍ ለጋሶች ለተራቡ ኢትዮጵያውያን የሚሰጠውን እርዳታ የኢትዮጵያ መንግስት ከክልል መንግስታት ጋር በመቀናጀት በከፍተኛ ሁኔታ ለመዝረፍ መዘጋጀቱን አረጋግጫለሁ ብሏል። መረጃውን ሮይተርስና ዋሽንግተን ፖስትን የመሳሰሉት አለምአቀፍ ሚዲያዎች እየተቀባበሉት ይገኛሉ ! ከዚህ ቀደም የአለም የምግብ ፕሮግራም ሲል ፥ የገዛ ዜጎቹ ዳቦ አጥተው እየተራቡና እያለቁ > ብሎ በዶላር የቸበቸበው የሚለውን ዜና ሰምተን ስንገረም ፥ ጉደኛው መንግስታችን ዛሬ ደግሞ ፦ > የሚለውን ዜና በአለምአቀፍ ሚዲዲያዎች ሲነገርለት መስማት በራሱ የህሊና ሰላም ያሳጣል! ምን አይነት አረመኔነት ነው ግን ? ምን አይነት ሞራለ ቢስነትስ ነው? ኧረ የእናንተስ ከፋ! 4.0K views20:20