Get Mystery Box with random crypto!

የጉድ ሀገር ገንፎ እያደር ይፋጃል! > USAID በሚሊዮን ለሚቆጠሩ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለ | ዘሪሁን ገሠሠ

የጉድ ሀገር ገንፎ እያደር ይፋጃል!

<< ሌባ ሁላ ፣ ሌባ ሁላ ...! >>

USAID በሚሊዮን ለሚቆጠሩ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለሚሹ ኢትዮጵያውያን የሚያደርገውን የምግብ እርዳታ ፣ በመንግስት ከፍተኛ ሌብነትና የዘረፋ እቅድ ምክንያት ለጊዜው ሙሉ በሙሉ ማቋረጡን ገልጿል!

የዩናይትድ ስቴትስ አለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅት (USAID) ዛሬ ይፋ ባደረገው መግለጫው ፣ ከመንግሥት ሾልከው በወጡ ሰነዶች ፣ ከአለምአቀፍ ለጋሶች ለተራቡ ኢትዮጵያውያን የሚሰጠውን እርዳታ የኢትዮጵያ መንግስት ከክልል መንግስታት ጋር በመቀናጀት በከፍተኛ ሁኔታ ለመዝረፍ መዘጋጀቱን አረጋግጫለሁ ብሏል።

መረጃውን ሮይተርስና ዋሽንግተን ፖስትን የመሳሰሉት አለምአቀፍ ሚዲያዎች እየተቀባበሉት ይገኛሉ !

ከዚህ ቀደም የአለም የምግብ ፕሮግራም <<በኢትዮጵያ አሳሳቢ የረሀብ አደጋ ላይ ለሚገኙት ቀሚሊየኖች ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እርዳታ ላድርግ!>> ሲል ፥ የገዛ ዜጎቹ ዳቦ አጥተው እየተራቡና እያለቁ << ስንዴውን ከእኔ ግዙኝ! >> ብሎ በዶላር የቸበቸበው የሚለውን ዜና ሰምተን ስንገረም ፥ ጉደኛው መንግስታችን ዛሬ ደግሞ ፦

<< የሚላስ የሚቀመስ አጥተው በጠኔ እየረገፉ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ለመመገብ ከአለም መንግስታት የተደረገ እርዳታን የገዛ መንግስታቸው እየዘረፈ በማስቸገሩ ተቋረጠ! >> የሚለውን ዜና በአለምአቀፍ ሚዲዲያዎች ሲነገርለት መስማት በራሱ የህሊና ሰላም ያሳጣል! ምን አይነት አረመኔነት ነው ግን ? ምን አይነት ሞራለ ቢስነትስ ነው?

ኧረ የእናንተስ ከፋ!