Get Mystery Box with random crypto!

የታሰሩበት ከታወቀው ይልቅ ታፍነው ደብዛቸው የጠፋው በርካቶች ናቸው ! ይህ ወጣት እንዳልካቸው | ዘሪሁን ገሠሠ

የታሰሩበት ከታወቀው ይልቅ ታፍነው ደብዛቸው የጠፋው በርካቶች ናቸው !

ይህ ወጣት እንዳልካቸው እሸቱ እጅጉ ይባላል።

በሸገር ትራንስፓርት ውስጥ የስምሪት ክፍል ሀላፊና ምስጉን ሰራተኛ ነው። ሚያዚያ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ስድስት ኪሎ አካባቢ ከሚገኘውና ተከራይቶ ከሚኖርበት መኖሪያ ቤቱ ፣ የፌደራል ፓሊስ ልብስ የለበሱና አምቡላንስ መኪና የያዙ የፀጥታ ሀይሎች አፍነውት መሰወራቸውን አከራዬቹና በአካባቢው ያዩ ግለሰቦች ተናግረዋል።

ከዚያን እለት ጀምሮ ወጣት እንዳልካቸው የት እንዳለ ለማወቅ አልተቻለም። ቤተሰቦቹም በየ ፀጥታ ተቋሙ ቢያመለክቱና ቢጠይቁም እስካሁን ‘’ አየን’’ የሚል መንግስታዊ አካል አልተገኘም። ወላጆቹ በከፍተኛ ጭንቀትና ህመም ላይ ናቸው።

የዜጎችን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ተቀዳሚ ሀላፊነት ባለበት ‘’መንግስት ነኝ ‘’ በሚለው አካል ይህን መሠል የጋንግስተር ተግባር እየተፈፀመ ወደማን አቤት ይባላል ?

በአዲስአበባና በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በመንግሥት፣ የፀጥታ አካላት በተለመደው ሁኔታ ተይዘው ከሚታሰሩት አስርት ሺዎች ውጭ በድብቅ እየታፈኑ ለወራት አድራሻቸውና ያሉበት ሁኔታ የማይታወቅ ዜጎች ቁጥር እጅግ በጣም አሳሳቢ እየሆነ ነው!

አሳዛኝና በሀገራችን ለመኖር ዋስትና ባሳጣን ፋሽስታዊ ስርዓት ላይ ወድቀናል!

#ሼር በማድረግ በአንባገነኖች ታፍነው ደብዛቸው ለጠፋ ወገኖቻችን ድምፅ እንሁን !