በደቡብ ወሎ ሀይቅ ከተማ አስተዳደር በርካታ ወጣቶች ለእስር መዳረጋቸው ተገለፀ! በዛሬው እለት ከያሉበት እየታደኑ ለጅምላ እስር ከተዳረጉት መካከል ፦ - አቶ ብርሃን አበራ ይመር - መ/ር መሀመድ ይማም - አቶ ዘርአይ እንድሪስና ሌሎች በርካቶች ይገኙበታል፡፡ ሌሎች ያልተያዙና በስም ዝርዝር ተይዘው እየተፈለጉ ያሉ ወጣቶች መኖራቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ወጣቶቹ እስካሁን የታሰሩበት ምክንያት በውል ተለይቶ ባይታወቅም ፥ በተያዙበት ወቅት "ህዝብን ለአመፅ ቀስቅሳችኃል!" የሚል አመክንዮ እንደቀረበላቸው ከስፍራው ያገኘሁት መረጃ ያመለክታል፡፡ በተለያዩ አካባቢዎች የጅምላ እስርና አፈና ተባብሶ መቀጠሉንም መረጃዎች ያመለክታሉ! 11.8K viewsedited 20:06