ፍዝ ተመልካች ስትሆን ተመሳሳይ አክተሮች ይተውኑብሃል! ደበበ እሸቱ የሰላምም የጦርነትም ሌክቸር እንዲሰጥህ ያደረከው ፥ ከመቶ ሚሊየን በላይ ሆነህ ፥ ሀገሪቱን መቶ የማይሞሉ ካንሰሮች በተመሳሳይ አዙሪት ውስጥ እየተሽከረከሩ እንዲፈነጩባት ምቹ ሁኔታ ፈጥረክ በመስጠትህ ነው! በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የእያንዳንዳችን አስተዋጽኦ አለበት! ብሮ ፦ አልሰማኸውም እንዴ ዛሬ > ብሎ ሲሳለቅብህ? አንተኑ አዋግቶ ፥ አጫርሶና አፋጅቶ በሀዘንና በሰቆቃህ ላይ " ከልብ ተራረቅን ይሉሃል! እኛ ደግሞ ተላልቀን ፥ ተራርቀንና ተሸማቀን ፥ ዛሬም በብስቁልናና በመከራችን ላይ ፥ የመከራ ምንጮቻችንን እያፀደቅን ስንናከስ ቀጥለናል ...! ህዝብ ለህዝብማ ከልብ እንዲተራረቅ ፥ እንዲቀራረብና እነሱ የዘሩትን የጥላቻ ትርክት ነቅሎ አብሮነቱን እንዲያስቀጥል ፈፅሞ አይፈልጉም ! ምክንያቱም መደበቂያ ዋሻቸው ነዋ! "አብይ አህመድ አለምአቀፍ ወንጀለኛ ነው!" ስትል " ይህ የኦሮሞ ጥላቻ ነው!" ብሎ የሚደበቀው በምስኪኑ የኦሮሞ ህዝብ ነው፡፡ "ጌታቸው ረዳ የትግራይ ወጣቶችን አስፈጅቶ የህዝብ ስልጣን ላይ ያለ ወንጀለኛ ነው!" ብለህ ብትታገለው ፤ " ይህ የትግራዋይ ጥላቻ ያሰከራቸው የአሀዳውያን ዘመቻ ነው!" ብሎ ከለላ የሚያገኘው በዚሁ በሚያናክሰው መከረኛ ህዝብ ነዋ! የሴራ ፖለቲከኞቹ በህዝብ ፍቅር የሚከስሩና የሚከስሙ ሲሆኑ የሚለመልሙት ደግሞ በሚዘሩት የጥላቻ ፍሬ ህዝብ ለህዝብ ተናክሶ ፥ የሴራ ወጥመዳቸው ሰለባ ሲሆን ብቻ ነው! ሌላ ሌላውን ተወው "ድራማ" ነው! ስር-ነቀል የአስተሳሰብ ለውጥና የትግል ጅማሮ ውስጥ መግባት ካልቻልን ፥ የኢትዮጵያና የህዝቦቿ እጣፋንታ ከዛሬው የነገው እጅግ ይከፋል! ሠላም! 4.9K viewsedited 19:55