የተሻለ ሀሳብ ዋጋ በማያወጣበት ሀገር ውስጥ ሁሉን ነገር ለማድረግ የሚያስችልህ ስልጣንና ገንዘብ ብቻ ነው! ስልጣንና ገንዘብ ካለህ ፥ " ምሁር ፥ አዋቂና የሁሉ ነገር አድራጊ ፈጣሪ" ተደርገህ ትቆጠራለህ፡፡ የሚያስቅ ሳትናገር ይሳቅልሀል ፤ ለማይረባ ሀሳብህ ይጨበጨብልሀል ፥ አጀብህና ተከታይህ ብዙ ይሆናል፡፡ የተሻለ ሀሳብ ማራመድና ወደተሻለ ከፍታ መውጣት አይታሰብም፡፡ "ባለህበት እርገጥ ብቻ! በአንድ ክብ ዙሪያ መሽከርከር....! በአስመሳይነት ፥ በአላዋቂነት ፥ በክፋትና በሴራ የተካኑት የትውልዱን ነገ ከጫማቸው ስር እየተረገጡ ሲጫወቱበት መመልከት ብቻ! በዚህ አይነቱ አውድ "ብዬ ነበር...!" ማለት እጣፋንታህ ይሆናል! ከዚህ አውድ ለመመንጠቅ ያለው ብቸኛ መንገድ ፤ ከተናጠል ለቅሶና ቁዘማ ወጥቶ ፤ በተደራጀ ሀሳብና አላማ ፤ በህብረትና በአንድነት መራራ ትግል ማድረግ ብቻ ነው! 4.5K views19:12