Get Mystery Box with random crypto!

ከላይኛው የቀጠለ… ቦለጢቃ የሚጠመቁት። '…ሰሞኑን በየከተማው በሰሜኑ ጦርነት አሳብበው ዐ | Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

ከላይኛው የቀጠለ… ቦለጢቃ የሚጠመቁት።

"…ሰሞኑን በየከተማው በሰሜኑ ጦርነት አሳብበው ዐማራንም ትግሬንም ያፍሳሉ። ከምላሴ ጠጉር ይነቀል። ዐማራ ከፌደራል መሥሪያ ቤቶች በሙሉ ተለቅሞ ይወጣል። የኦሮሙማው ኃይል የአዲስ አበባን ባለቤትነት ለማረጋገጥ የሚቻለኝ በአዲስ አበባ የተከማቸውን የዐማራ ሕዝብ ቁጥር ማጥፋት መቀነስ ስችል ነው በማለት በጀመረው መንገድ የዐማራን ርስቱን፣ ታሪካዊ አሻራውን በሙሉ ይንዳል። ያፈርሳል። ያፈናቅለዋልም። ከሥራ ገበታውም ጠልዞ ያባርረዋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ጨምሮ የፌደራል መሥሪያ ቤቶች በሙሉ በፌደራል ፖሊስ የታዘዘ ነው በሚል ሁሉም የፌደራል መሥሪያ ቤቶች "ብሔራቸውን" እንዲሞሉ የተላከላቸውን ፎርም ደርሶኝ አይቼዋለሁ። እናም ዘጸአት የሆነ መፈናቀል በኦሮሙማው በኩል ዝግጁ ሆኖ ይጠባበቃል።

"…ሁሉም ክልል ሊበላ የተዘጋጀ እንደሆነ በማወቅ መከላከያው ውስጥ የሚገኙ ወታደሮች ጭምር አሁንም አልረፈደም ወደ ፋኖ ትግል በመቀላቀል ሀገሩንም ማዳን ራሳቸውንም ማትረፍ ይችላሉ። ያ ሲሆን ህወሓት በዚያው ትቆማለች። አቢይም ዐማራን ቀርጥፎ በልቶ ትግሬ ላይ መልሶ የማጣሪያ እኘካ በመፈጸም ወደ ሌላ ክልል በሻሻ ወደ ማድረጉ አይሄድም። ስልጤም ህወሓት ወደ ውጊያው ከገባች የወሎና የጎጃም፣ የጎንደር ዐማሮችን በሃይማኖት ስም መርዝ እየጋተ በገንዘብ እየረዳ ዐማራ ላይ ማዝመቱን ያቆማል። ብዙም ኃይል አይኖረውም። አቢይ አሕመድ ፋኖ ሊውጠው ሲደርስ የፋኖን ቀጣይ ዕቅድ በነመሳይ መኮንን በኩል እያስጠና፣ የፋኖ ቀጣይ ዕቅድም ምስጢር ስለማያውቅ ሃላል ስለሆነ ህወሓትን አላማጣን ከማሲያዙ በፊት የኦነጉን በቴን ገድሎ ኦሮሞ በራሱ አጀንዳ ተወጥሮ፣ ራሱን በቀበቶ አስሮ ፌስቡክ ላይ እየተንደባለለ እንዲያለቅስ አድርጎ ቁማሩን በሚገባ በጥንቃቄ ያስኬደዋል።

"…ዐማራ ከትግሬ፣ ትግሬ ከዐማራ፣ ኦሮሞ ከዐማራ እንዲናቆሩ ሒሳቡን ሠርቶታል። ኦሮሞ ወሎን የራሱ ለማድረግ ወሎ ከትግሬ ጋር መዋጋት አለበት። ትግሬ ለጊዜው በራያ ላይ ለሀጩን ቢጥልም በዐማራ ጥላቻ የታወረው ትግሬ የኦሮሚያ ካርታ ራያንም አጠቃልሎ እንደተዘጋጀ ማወቅም፣ ማየትም አይፈልግም። ኦሮሞ አቢይን እንዲያግዝ አውራ ጎዳናን ወደ ኦሮሚያ ክልል አጠቃልሎ አስገብቶለታል። ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ሲናና ሸዋሮቢት ሲቀር ሌላው ለኦሮሚያ ለማካለል የሰሜን ሸዋን ሕዝብ የማያባራ ጦርነት ውስጥ አስገብቶታል። ቤቱ፣ ንብረቱ፣ እርሻው ወድሞ፣ ከብቱን እየነዳ በግፍ ወስዶበታል። ዘመቻ ወሎን የኦሮሞ ቲክቶከሮች ሳይቀሩ ዋይዋይ የሚሉበት ነው። ኦሮሞ አዲስ በመጣለት የመሬት ደስታ ምክንያት አቢይን በፋይናንስም ህውሓትን በፕሮፓጋንዳ በማሞካሸትም እየደከመ ነው። የኦሮሞ አክቲቪስት አሁን ተጋሩ ጀግና! ደቡብ እና እኛ አንድ ነን! አገው እና ቅማንት ኩሽ ናቸው! የሚሉት ለመብላት ሲያዘናጓቸው ነው። የፖለቲካው ቅማንትም፣ የፖለቲካው አገው ሸንጎም ሁለቱም ጥገኞች በራሳቸው ምንም ማረግ የማይችሉ መሆናቸውን ስለሚያውቁ እንደ እስስት እየተቀያየሩ ያጃጅሏቸዋል። ቆይቶ አይሸነፍም እንጂ ዐማራ ቢሸነፍ በግሬደር ሰብስቦ በአንድ ጉድጓድ ነው የሚቀብሯቸው።

"…ስለዚህ ኦሮሙማው ሓሳብ ነው የፈጠረው። ይሄን ሓሳቡን ደግሞ ተግባራዊ ለማድረግ፣ ደቡቡም፣ አፋሩም ልቡ ወደ ፋኖ ከሆነ አቢይ ኦሮሞን ብቻ ይዞ ምንም ማድረግ አይችልም። ትግሬም የጎጃም ፋኖ የወታደራዊ አዛዦቹን ከፈታላቸው በኋላ ፋኖ ፋኖ ማለት መጀመሯ አደጋ ስለፈጠረበት ነው አሁን በቶሎ ራያን ያዙ፣ ግን ከዐማራ ፋኖ ጋር አታብሩ ብሎ ያዘዘው። የአባዲ ዘሙ ልጅ በፌስቡክ ገጹ ህወሓት ለዐማራ ፋኖ መሳሪያ እያቀረበች ነው ብሎ ከለጠፈ በኋላ ለገሰ ቱሉ ወጥቶ ህወሓት እየረበሸች ነው። የዐማራ ክልል ሰላም እንዳይሆን እየረበሸች ነው ብሎም መግለጫ እስከመስጠት ደርሶ ነበር። ሲገመገም ሕወሓት የምትፈልገውን ሰጥተን ከዐማራ ጋር መቆሟን እንድታቆም ማድረግ አለብን፣ ሁሉንም ከምናጣ አንዱን እንጣ ነው ነገሩ። ትናንት እንዳልኩትም መከላከያ ተብዬው ራያ አላማጣን አስተዳዳሪ ገድሎ ህወሓት እንድትገባ ካደረገ በኋላ ለገሰ ቱሉ ወደ ሚዲያ ወጥቶ ህወሓት የፕሪቶሪያውን ስምምነት ጥሳለች ብሎ ዋይ ዋይ እያለ አዛኝ ቅቤ አንጓች ሆኖ ይተውናል ባልኩት መሠረት ይኸው ዛሬ ወደ ሚዲያ ወጥቶ "ህወሓት የፕሪቶሪያን ስምምነት ጥሷል" እያለ ይፎግራል። ማፈሪያ።

"…ብልፅግና ስር እደሌለው ዛፍ ነው። ተቦርቦሮም ያለቀ ነው። ማድያት ፊቱን ወርሮት በሜካፕ ሸፍኖ የሚዘንጥ ነው ብልጽግና። ውኃ ሲነካው የሚለቅ ቡራቡሬ ነው ብልጽግና። ምስጥ በልቶት ሊወድቅ የደረሰ፣ ነገር ግን በቀለም ያማረ፣ በመብራት ያሸበረቀን ቤት ነው የሚመስለው። ብልጽግና እስስት ነው። መናፍቅ ከሃዲ ነው። ብልጽግና አራጅ ነው። የአውሬ ገባሪ ነው። ብልፅግና ውሸት ሀሰትም አይደለም። ራሱ የሀሰት ፈጣሪዋ ነው። በብልፅግና ሴራ መታለል፣ መሸወድ አይገባም። እያንዳንዱ የብልጽግና ሴራ ለዐማራ ፋኖ እንደ መልካም እድል መጠቀም ያስፈልጋል። ሁሉም ዐማራ ዓይኑን ከ4ኪሎ ላይ ማንሣት አይገባውም። ለወያኔ የራያን ፋኖ ብቻ ይዞ መግጠም ይቻላል። የብልፅግና ሴራ በፈጠጠ ቁጥር ዐማራው ይነቃል። በሰው ኃይል ሁላ ይደራጃል። ብአዴን ይፈርሳል።

"…በመጨረሻም ይህቺን ከትግሬ ቦለጢቀኞች ቤት የተገኘች የፖለቲካ ትንተና እና ግምት፣ ትንቢትም በሉት ደጋግማችሁ ታነቡት ዘንድ በመጋበዝ ርዕሰ አንቀጼን ልቋጭ።

"…የወዲ ወረደ የትላንቱ መግለጫ፣ የጌታቸው አጭር የፌስቡክ ጽሑፍ እና የዛሬው የዐማራ ክልል መግለጫ

"…የትግራይ ክልል መንግሥት ከብአዴን ጋር የተፈራረመው ምንም ዓይነት ውል የሌለ በመሆኑ የክልሉ መንግሥት በዐማራ ክልል መንግሥት መግለጫ ላይ ምላሽ ይሰጣል ብዬ ባላምንም. . .ይህንን በሚመለከት ግን በቅርቡ የፌደራል መንግሥቱ የሚሰጠው መግለጫ ምላሽ ሁሉን ነገር ግልፅ ያረገዋል የሚል እምነት አለኝ…!

"…የሆነው ሆኖ የብአዴን እና የወጣት ሊጉ አብን ከቀናት በፊት የሰጠው መግለጫ መመሳሰል የሚነግረን ነገር ቢኖር

1. የክልሉ መንግሥት በዚህ አጋጣሚ ድጋፍ ለማግኘት እና ወልቃይት እና ራያ ከጦርነቱ በፊት ወደ ነበሩበት ሲመለሱ እኔ የለሁበትም ወረራ ሰጠ! ወረራ ነሳ በማለት ከደሙ ንፁህ ነኝ ለማለት!

2 በብአዴን እና በፌደራል መንግሥቱ መሃል ምናልባትም የፕሪቶሪያ ስምምነቱ አፈፃፀም ላይ አለመግባባት መኖሩን

3.ወይም በክተት ሰበብ ተበትኖ በየቀበሌው በደፈጣ ያስቸገረውን የፋኖ አደረጃጀትን ወልቃይት እና ራያ ላይ ለመሰብሰብ እና በመደበኛ ውጊያ ለመደምሰስ

4. የትግራይ ክልል መንግሥት ልክ የዛሬ ዓመት ጌታቸው ረዳ አሜሪካ ከትግራይ የዲያስፖራው ማኅበረሰብ ጋር በነበረው ውይይት እንዳለው. . ''.የፌደራል መንግሥቱ በወረራ የተያዘብንን ግዛት በጉልበት እንድናስመልስ በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርብልንም. . ይህ ሃላፊነት የፌደራል መንግሥቱ በመሆኑ እና ከአቅሙ በላይ ይሆናል የሚል እምነት ስለሌለን አልተቀበልነውም! ነገር ግን ከአቅሙ በላይ ሆኗል ብለን ካመንን እና ጥያቄ ከቀረበልን ሕገ መንግሥታዊ ግዛታችንን ለማስመለስ አስፈላጊውን ትብብር ማድረጋችን አይቀርም'' እንዳለው በፌደራል መንግሥት ይሁንታ በወረራ የተያዙ ግዛቶችን በጉልበት የማስመለስ ሂደት ላይ መኮኑን መደምደም ይቻላል!

5. የመጨረሻው እና የመሆን ውስን አጋጣሚ ያለው ግምቴ ደግሞ የፌደራል መንግሥቱ በብአዴን በኩል ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ማስተላለፍ እና ሁኔታው… ከታች ይቀጥላል