Get Mystery Box with random crypto!

'ርዕሰ አንቀጽ' '…የበሻሻው አራዳ ልቡሰ ሥጋው ከሃዲ ውሸታም ደም አፍሳሹ እቡዩ አህመድ በሊቀ | Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"ርዕሰ አንቀጽ"

"…የበሻሻው አራዳ ልቡሰ ሥጋው ከሃዲ ውሸታም ደም አፍሳሹ እቡዩ አህመድ በሊቀ ሰይጣናቱ በክፉ ጨካኙ በዳንኤል ክብረት መሰሪ የይሁዳ ምክር ኖረውም የማይጠቅሙትን የዐማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድሩን አረጋ ከበደን ጨምሮ ለሱሙ ወሳኝ የሚባሉትን ዋና ዋኖቹን የዐማራ ክልል ባለ ሥልጣናት በፕሪቶሪያው የኦህዴድና የህወሓት ስምምነት መሠረት በፌደራል መንግሥቱ ይሁንታ በመከላከያው ድጋፍ "ህወሓት ራያ አላማጣ ወረዳዎችን በሚያስረክቧት ወቅት" እኛ በሀገር ውስጥ በልነበርንበት ጊዜ ነው" የሚል ምክንያት እንዲኖራቸው ለማድረግ በመምከር "በዐማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሚመራ የዐማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የቦርድ አመራሮችና የሚዲያ ሓላፊዎችን ያካተተ ልዑክ ከአፕሪል 12/2024 ወይም ከሚያዝያ 4/2016 ዓም ጀምሮ ለተከታታይ 16 ቀናት ለሥራ ጉዳይ በሚል ምክንያት ወደ ሰሜን አሜሪካ እንዲሄዱ ተደርገዋል። የዐማራው ወኪሎች በቆይታቸው ወቅት ወጪያቸውን የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት እንደቻላቸው የተነገረ ሲሆን ለቀን አበል የሚሆን የኪስ ገንዘብም ከዚያው ከፈረደበት የዐማራ ሕዝብ ኪስ ካቋቋመው ከአሚኮ በጀት ላይ ለእያንዳንዳቸው በዶላር እንዲከፈላቸው ነው የተደረገው ተብሏል። አሁን ሀገረ አሜሪካ እንዲሄዱ የተገደዱት የክልሉ ባለ ሥልጣናት ሄደው በላስ ቬጋስ ከተማ የሚገኙ ሲሆን በዚያም በቬጋስ በሸነና እያሉ እንደሆነ ነው የተሰማው። ላስቬጋስ ካዚኖ ቤት ተገብቶ 8 ሺ ዶላር ምን ልትጠቅማቸው ነው?

"…ቀደም ሲል አቢይ አሕመድ እነ አቶ ተመስገን ጥሩነህ ያሉበት ኮሚቴ በማቋቋም፣ አረጋ ከበደና ቡድኑ በአገው ሸንጎው በአቶ ሰማ ጥሩነህ ተጠርንፎ ህወሓት መጀመሪያ ራያን፣ ቀጥሎ ደግሞ ወልቃይትን እንድትረከብ ከህወሓት ጋር እንዲስማሙ አደረገ። ከሕዝቡ ለሚነሣብን ተቃውሞስ ምን እንመልሳለን ለሚለው ስጋታቸውም የተሰጣቸው መልስ "የዐማራ ሕዝብ ምንም አያመጣም። ትንሽ የአፍ ድለላ ማድረግ ብቻ ፀጥ ለማሰኘት በቂ ነው። ዐማራ ስለ ፍቅር፣ ስለ አንድነት ከተሰበከ ይሸነፋል። ይተወዋል። ስለ ዐማራ ሕዝብ እኛ አለን ስለ ሕዝቡ አታስቡ። ለእሱ እሱን ዝም ለማሰኘት እኛ በሚገባ ተዘጋጅተናል። አስቸጋሪ የሚሆኑ የዐማራ ብልጽግና ሰዎች ካሉም እርምጃ ይወሰድባቸዋል። የዐማራ ብልጽግና ሰዎች አኩርፈው የሚሄዱበት መጠጊያ እንዳይኖራቸውም ተደርጓል። እሺ ብለው ለእኛ ከታዘዙ መልካም እምቢ ካሉም ግን ወይ በእኛ አልያም በፋኖው ይበላሉ። እናም ስለ ሕዝቡ አታስቡ በማለት ነው ወደ አማሪካ የሸኟቸው። ንግድ ባንክም በታዘዘው መሠረት፦

1ኛ፦ ለአረጋ ከበደ የዐማራ ክልል መስተዳድር 8350$ 2ኛ፦ ለይርጋ ሲሳይ የአሚኮ ቦርድ ሰብሳቢ 8350$
3ኛ፦ ለአህመዲን መሐመድ የአሚኮ ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ 8350$
4ኛ፦ለመንገሻ ፋንታሁን የአሚኮ ቦርዳባል 7450$
5ኛ፦ሙሉጌታ ሰጥዬ የአሚኮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ 8350
5ኛ፦ለግዛቸው ሙሉነህ የአሚኮ አማካሪ 7450$
6ኛ፦ለተሾመ ውዱ የአሚኮ ምክትል ስራ አስፈጻሚ 6850$
7ኛ፦አንዳርጌ መዓዛ የርዕሰ መስተዳድር ፕሮቶኮል ሹም 6850$ ያህል ገንዘብ ነው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባህርዳር ቅርንጫፍ ከሚገኘው የኮርፖሬሽናችን የባንክ ሂሳብ ቁጥር ተቀናሽ ሆኖ ሰጥቷቸው "ጎሽ የእኛ አንበሶች፣ መልካም የበሸነና ጊዜ ይሁንላችሁ። አቶ ገዱን ካገኛችሁት በዚያው ሰላም በሉልን በማለት ነው የሸኟቸው።

"…በትናንቱ የምሥራቅ ዐማራ ፋኖ መግለጫ በተራ ቁጥር 1 ላይ እንደተጠቀሰው "የዐማራ ሕዝብ በብአዴን መሪነት የሚመጣ ውርደት እንጅ ነጻነት የሌለ መሆኑን ካወቀ ውሎ አድሯል፡፡ ይሁን እንጅ በዋና ዋና ከተሞች የሚታየው መዘናጋት ዋጋ የሚያስከፍለን በመሆኑ ዘላቂ ነጻነቱን ለማረጋገጥ ፍጹም መራራ ትግል በማድረግ ትግሉን ማቀጣጠል አለበት፡፡ የዐማራ ሕዝብ በመስዋዕትነቱ ወደእናት ግዛቶቹ የመለሳቸውን እነ ራያ ወልቃይትን አሳልፎ እየሰጠ ያለውን ብአዴን፣ ገጠር ከተማ ሳይል የፈራረሰ መዋቅሩን ጨርሶ ግብዓተ መሬት ለማስገባት ሁሉም በያለበት እንዲፈንን (ፋኖ እንዲሆን) የትግል ጥሪያችንን እናቀርባለን በማለት የጠቀሱትንም የምንመለከተው የብአዴንን አይረቤነት ሁሉም የሚረዳው መሆኑን ነው።

"…የሚገርመው ደግሞ እነ አረጋ ከበደን በላስቬገስ ተቀብሎ እንዲያስተናግዳቸው በአቢይ አሕመድ የታዘዘው ግለሰብ ኤርትራዊ ባለሃብት መሆኑ ነው። ሻአቢያ፣ ወያኔ እና ብልፅግና አሁንም ቁማር ላይ ናቸው ማለት ነው። ከድሮ ጀምሮ ከጥንትም ሁሌ እንደምለው "የመለስ ዜናዊን ቡድን የበሉት ሻአቢያ፣ አቢይ አሕመድና የዓድዋው ወያኔ በመጨረሻ ግንባር እየፈጠሩ መገለጣቸው እውን መሆኑን ነው። የዋህነት ብቻ ሳይሆን በብዙ ደንታ ቢስ፣ ዳተኛ፣ ቸልተኛ፣ ሰነፍ ጅልነት እና ፈሪ ቦቁባቃ የተሞላው የዐማራ ቦለጢቀኛም የሚሆነውን እያየ አፉን ለጉሞ ተቀምጧል። አሁን ላይ ምድር ላይ ያለው ዐማራ ጥሩ ነው። አየር ላይ ያለው ዐማራም አሁን ከበፊቱ የተሻለ ቢሆንም አሁንም ግን ይቀረዋል። ዐማራም እንደ ትግሬ እና ኦሮሞ ቦለጢቀኞች ጨካኝ፣ ከሃዲ፣ አረመኔ ካልሆነ በቀር ሕዝቡን በቀላሉ መታደግ የሚችል አይመስለኝም።

"…የራያው ወረራ በዚያ የሚቆም አይደለም። አይቆምም። ጠለምት፣ ከዚያ ወልቃይት ልክ በራያው መንገድ ነው ከዐማራው ፈልቅቀው ለመውሰድ የተዘጋጁት። ብልጽግናን አምነው በራያ፣ በወልቃይት እና በጠለምት ከሕዝባቸው ወኪል ከዐማራ ፋኖ ጋር የተቀያየሙ በሙሉ የሚጠብቃቸው ሞት ብቻ ነው። ካልሸሹ ወያኔ፣ ከሸሹ ብልፅግና ይገድላቸዋል። የሚሞተው የብልፅግና ባለ ሥልጣን ዐማራ ስለሆነ ችግር የለም። ዐማራ ብልጽግና ሆነ፣ ብአዴን ሆነ፣ አብን ሆነ፣ ተራ ሕዝብ ሆነ ሞቱ ጣጣ አያመጣም። ለዚህ ነው ብልፅግናን አምኖ የራያ አስተዳዳሪ ሆኖ የሄደው የደብረታቦር ዩኒቨርስቲው አቶ ደርበው፣ የቅርብ ጊዜ ሙሽራው የጫጉላ ጊዜውን ያልጨረሰውን ሰው የህወሓትን ወደ ራያ መግባት ተከትሎ የደፉት፣ የገደሉት። በዚህ ሰው ሞት ሚስቱና ቤተሰቦቹ ያዝናሉ። ህወሓት እና ብልፅግና ይደሰታሉ። በሰውየው ሲሳደድ የኖረው፣ የከረመው ፋኖም ሥራው ያውጣው ባይ ነው። ደመ ከልብ በሉት። ይኸው ነው ወልቃይት ላይም የሚከሰተው። መዝግቡልኝ። 

"…ከዚህ ተነሥቼ ለዐማራ የእኔ የዘመዴ ምክር የሚከተለው ነው። ዐማራ በቀጣይ ከፊቱ ብዙ የጦር ግንባሮች ከብዙ ኃይሎችም ጋር ከባድ ጦርነት ይገጥመዋል ብዬ እጠብቃለሁ። ለሁሉም የጦር ግንባሮች ግን እኩል መዘጋጀት ይኖርበታል። ዐማራ ሰፊም ጀግናም ሕዝብ ስለሆነ ከተናበበ አሸናፊነት የእጁ ነው የሚሆነው። ዐማራ ከበፊቱ በተሻለ ቁመና ላይ እንደሚገኝ የታወቀ ነው። እንደ በፊቱ በጥቂት ሰዎች የሚታገል አይደለም። በሀገረ መንግሥቱ ተስፋ የቆረጠ እና ወደ አባት ሀገር ዐማራ ፊቱን ያዞረ ዕልፍ ዐማራ የዐማራ ትውልድ ስለተፈጠረ አያሳስብም። ፈተናው እንዳለ የተረዱ ምሑራን፣ ነጋዴዎች፣ ተማሪዎች፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ገበሬዎች፣ የመከላከያ፣ የፌደራል ፖሊስ አባላት፣ የዐማራ ልዩ ኃይል እና ሚኒሻዎች የዐማራ ፋኖን ተቀላቅለው ዐማራ ትግሉን በብረት ጀምሯል። እናም ገና ለጋው የዐማራ ትግል ገና ከአሁኑ ሀገሪቷን ሽባ አድርጓት ተገኝቷል። መሀል ሰፋሪው፣ ሰነፉ፣ ደንታ ቢሱና ባንዳው ዐማራም ሲመርረው ትግሉን መቀላቀሉ አይቀርም። እናም ዐማራ ውሎ ሲያድር ወጥሮ በመመከት ሃቅ ስላለው ሁሉንም ጠላቶቹን ያሸንፋል። እኔ በዐማራ መቼም ተስፋ አልቆርጥም። የጦር ግንባሮቹንም እጠቅሳለሁ።

ሀ፦ ሰሜን ወሎ ራያ … ከታች ይቀጥላል…