Get Mystery Box with random crypto!

ዜና እስር…!! '…ደህና እደሩ ካልኩ በኋላ የመለሰኝ የእስር ዜና ነው። አንዳንዶች ነጭ ነጯን | Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

ዜና እስር…!!

"…ደህና እደሩ ካልኩ በኋላ የመለሰኝ የእስር ዜና ነው። አንዳንዶች ነጭ ነጯን መስማቱ ባይመቻችሁም እኔ ግን ብሶብኝ ቀጥያለሁ። ብልፅግናዎች በተለይ እኔ ፔጅ ላይ የሚጻፈውን ባታዩት ሁላ ትመርጣላችሁ። እኔ ፔጁን የከፈትኩት ድምፅ ለሌላቸው ድምፅ ልሆንበት ነው። ነጭነጯን ብቻ።

"…ዛሬ ጠዋት የኦሮሚያ መዝሙር አንዘምርም፣ የኦሮሚያ ባንዲራም አንሰቅልም ያሉና በቂርቆስ ክፍለከተማ የፈለገ ዮርዳኖስ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ተቃውሞ ተከትሎ የአዳነች አቤቤ መንግሥት ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 9:00 ሰዓት ወደ ትምህርት ቤቱ ፎሊስ በመላክ የትምህርት ቤቱን ርዕሰ መመህር ጨምሮ ሌሎች መምህራንን ወደ ዘብጥያ ማውረዱ ተሰምቷል።

"…በኦሮሚያ  ባንድራ የተነሳ የትምህርት ቤቱን  ዳሬክተሮችን እንዲሁም 3 መምህራኖችን ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ በፖሊስ ተይዘው አሁን ያሉበት ዘብጥያ እዚያው ቂርቆስ ክፍለ ከተማ በፖፖላሬ ፖሊስ ጣቢያ ሲሆን ፖሊስ ቃላቸውን ሳይቀበል በጣቢያው እንዲያድሩ እንዳደረጋቸውም ተስምቷል። አሁን ዘብጥያ ወርደው ያሉት ዋና ርዕሰ መምህር አቶ ኤርሚያስ፣ ምክትል ርእሰ መምህር አቶ እስጢፋኖስ፣ አቶ አለሙ እና ሌሎች 3 መምህራኖች በአዳነች አበቤ ትእዛዝ ተይዘው ወደ ዘብጥያ ወርደዋል። ዋናው ክሳቸው ሌሎች የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና መምህራን ትእዛዝ ተቀብለው ሲፈጽሙ በዚህ ትምህርት ቤት የሚማሩ ተማሪዎች ምን ብላችሁ ብታስተምሯቸው ነው ከኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማና መዝሙር ጋር እንዲህ የተጣበቁት የሚል ክስ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የአዲስ አበባ ህፃናት ከኦህዴድብአዴንኦነግ በለጡ እኮ።

• ኧረ ሰከን በል ኦህዴድ…!!