Get Mystery Box with random crypto!

የተማሪዎች መደፈር እና የሞት ዜና…!! '…በደብረ ታቦር እና በባህርዳር ዩኒቨርስቲ የማኅበራዊ | Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የተማሪዎች መደፈር እና የሞት ዜና…!!

"…በደብረ ታቦር እና በባህርዳር ዩኒቨርስቲ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪ የዐማራ ሴት ታዳጊ ህፃናት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በፀጥታ ኃይሎቹ የፌደራል ፖሊስ አባላት መደፈራቸው ተሰምቷል። በረብሻው ወቅት የሞቱም አሉ። "…ከዱር ቤት ሰሜን አቸፈር ባህርዳር ለፈተና የሄዱ አምስት ህፃናት ተማሪዎች በንዘልማ ካምፓስ አምስት ታዳጊ የገጠር ልጆች በተለይ ባህርዳር የተደፈሩትን ዩኒቨርስቲው እያከመ፣ ኪኒን እና መርፌ የሰጠ ለፈተና ያቀርባቸው እንደነበርም ተሰምቷል።

"…በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ፖሊሶቹ በርካታ ተማሪዎችን የደፈሩ ሲሆን በተለይ የብጥብጡ መነሣት ለፖሊሶቹ ምቹ የመድፈር ሁኔታን እንደፈጠረላቸውም ነው እማኞቹ የሚናገሩት። የደብረታቦሮቹ የደቡብ ጎንደር ተማሪዎች አሁን ያሉበት ሁኔታ የማይታወቅ ሲሆን በባህርዳር ዘንዘልማ ካምፓስ ታፍነው የተደፈሩት ታዳጊዎች እስከአሁን ወደ ቤተሰቦች ያለመሸኘታቸው ታውቋል። "…ይሄ ደግሞ ግፍም፣ ኃጢአትም፣ ነውርም፣ ጭካኔም፣ ወንጀልም ነው። ችግሩ ተደፋሪው ተቆርቋሪ አልባው ዐማራ መሆኑ ነው።

"…በአዲስ አበባም በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዮኒቨርስቲ  የሁለት የዳግማዊ ሚኒሊክ ትምህርት ቤት ሴት ተማሪዎች መገደልም እየተነገረ ነው። እየቆየ ሲመጣ የሚወጡ አስደንጋጭ ዜናዎች እንደተጠበቁ ሆኖ ሚንስትር መስሪያ ቤቱ በቀጣይ ላለው ፈተና ፌደራል ፖሊሶቹ ህፃናትን እንዳይደፍሩ የሆነ ነገር ቢያደርግ መልካም ነው እላለሁ።

"…ደኅና እደሩ…!!