Get Mystery Box with random crypto!

ኦነግ ሽሜ በኢሉአባቦር…!! '…ኦነግ ሽሜ በደሌ ከተማ አፍንጫ ስር ከበደሌ በቅርብ ርቀት ላይ ያ | Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

ኦነግ ሽሜ በኢሉአባቦር…!!

"…ኦነግ ሽሜ በደሌ ከተማ አፍንጫ ስር ከበደሌ በቅርብ ርቀት ላይ ያለችዋን ጨዋቃ ከተማን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሮ ሲዋጋ መዋሉ ተነግሯል። የኦሮሚያ ፖሊስ ልዩ ኃይሎች ለመዋጋት ቢሄዱም እንደድሮው ፖሊስ ሲያይ የሚሸሽ ኦነግ ሽሜ አይደለም የገጠማቸው። እጅግ ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ ከባድ ኃይል ነው የገጠማቸው። ክላሽ ይዞ የሄደ ፖሊስ ነፍስ ይማር።

"…በዛሬው የጨዋቃ ላይ ውጊያ እስከአሁን ብዙ የኦሮሚያ ፖሊስ አባላት መገደላቸው፣ መቁሰልና መማረካቸውም የበደሌ የወሬ ምንጮቼ ነግረውኛል። ጨዋቃ ላይ እስከአሁን የሞተው በቁጥር አልታወቀም። የጨዋቃ ሕዝብ በአብዛኛው ተሰዶ በደሌ መጥቷል። ሊዋጋ ከሄደው የኦሮሚያ ፖሊስ መካከል እስከአሁን ቆስሎ እንኳ የተመለሰ አላየንም ነው የሚባለው። መኪናም፣ መሳሪያም ለኦነግ በምርኮ ስም ገብቶለታል። 

"…ዛሬ ረቡዕ ነው። የበደሌ ነጋዴዎች 77 የምትባል ወረዳ ረቡዕ ረቡዕ ሂደው ይነግዳሉ። 77 ለበደሌ በጣም ቅርብ ስፍራ ያለች የገጠር ከተማ ናት። ዛሬም ነጋዴዎች ለሥራ ሄደው ነበር። እናም ጠዋት ላይ ኦነግ ሽሜ ወደ ከተማዋ በመግባቱ ነጋዴዎቹ አምልጠው ወጥተዋል። በወለጋም ውጊያው ቀጥሏል።

"…በሰሜን ትግራይ በምዕራቡም በኩል ወደ ትግራይ የኢትዮጵያ ጥምር ጦር እየገፋ እንደሆነ የተነገረ ሲሆን በራያ በኩል ከትግራይም ከጥምር ጦሩም ብዛት ያለው ተዋጊና ከባድ የጦር መሣሪያዎችም መሰለፋቸው ተሰምቷል። ህወሓት ወደ አፋርም የተዋጊ ኃይል ማስጠጋቷም ተነግሯል። የህወሓትን መዳከም ያየችው አማሪካም ሩሲያ በአስመራ በኩል ሳትቀድመኝ በአውሮጳ ኅብረት በኩል ወልቃይት ላይ ልስፈር እያለች ነው። በሁለት ሀያላንና በ7 ዓረብ ሃገራት የሚባል ንግርትም አለ። ከኦሮሚያ በኩል ዝም ነው። ብአዴን ልጆቹን አስሮ ይሸልላል።

• ከበደሌ ጅማ ስንት ኪሎሜትር ይሆን…?