Get Mystery Box with random crypto!

ደግሞ መጣሁ…!! '…በፍኖተ ጽድቅ' ጉዳይ ብዙ ሰው ምርትነሽ ላይ ብቻ አፉን ሲከፍት አያለሁ። | Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

ደግሞ መጣሁ…!!

"…በፍኖተ ጽድቅ" ጉዳይ ብዙ ሰው ምርትነሽ ላይ ብቻ አፉን ሲከፍት አያለሁ። እኔ ግን ምርትነሽ ለምን በዚያ አዳራሽ ተገኘች የሚል ጥያቄ አላነሣሁም። አልጠይቃትምም። ጠሪው እኮ ሃብታም ነው። በዘመነ ህወሓት ጉራጌ፣ አሁን ደግሞ ኦሮሞ ነኝ የሚል ዲታ፣ ሃብታም እኮ ነው። ጠሪው እኮ ፋብሪካ ያለው ሰው ነው። የሮዳስ ቀለም ፋብሪካና የሮቶ ፋብሪካ ባለቤት። እነ በጋሻውና እነአሰግድ የጋጡት፣ መጨረሻ ላይ አኞው ሲቀር የአቡበከር ልጅ ከመተሃራ መጥቶ የተረከበው ባለሃብት ነው። በእኛ ቤት ደግሞ ለባለሃብት ያለን አክብሮት፣ ፍቅርና አድናቆት የታወቀ ነው። ደሀን ይጭነቀው እንጂ ለሃብታም ቀን በቀን ጠበል ቢረጭለትስ? ምንሺጊር?

"…እደግመዋለሁ እኔ ምርቴን የተቸሁት ለምን ወደ አዳራሹ ሄደች ብዬ አይደለም። አቡነ ሳዊሮስ እዚያ ተገኝተው እየባረኩ፣ አቡነ ዮሴፍ፣ አቡነ መቃርዮስ እዚያ ተገኝተው እየባረኩ፣ መምህር ጳውሎስ፣ መምህር ብርሃኑ አድማስ ከማኅበረ ቅዱሳን፣ ተስፋዬ ሞሲሳ፣ ዘማሪ ቴዎድሮስ፣ ዘማሪ እንግዳወርቅ በቀለ፣ ዘማሪ በሱፍቃድ፣ ዘማሪ ልዑልሰገድ ቋንቋዬነሽ፣ ዘማሪት አዜብ ከበደ፣ እነ ዘማሪ ማንትስዮና እነ መምህር ቅብጥርስዮ በአዳራሹ ተገኝተው እሷ ለምን ተገኘች ብሎ ሄጵ ማለት ግፍም፣ ነውርም፣ ወንጀልም፣ ኃጢአትም ነው። እኔ ምርቴን ያልኳት የቆዩ እና የተከበሩ መዝሙራትን እንደ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ቆማምጠሽ፣ ሰባብረሽ አትጣዪ ነው። ቢያንስ የቀደሙ መዝሙራት እንኳ እንደተከበሩ ለትውልድ ይተላለፉልን ብዬ ነው የተማጸንኳት።

• አህያውን ፈርቶ ዳውላውን ይል ነበር አጎቴ ሌኒን። ሌሎቹን መውቀሱ ቢከብዳችሁ እንኳ ምርትነሽን ብቻ መርጦ መቀጥቀጡ "ኢዴየቢራል"። ሼም ነው። ምርትነሽ ቢያንስ ልምድ አላት ጠፍቶ የመመለስ፣ ይቅርታም የመጠየቅ። በቃ ተፋቷት።

"…ሂኢ… !!