Get Mystery Box with random crypto!

'…የአይጥ ምስክሯ… '…ኦቦ ተስፋዬ ይሄ አምቡላ መጋፊያ አረቄ ቤት አይደለም። እንከባበር። | ዘመድኩን በቀለ(ነጭነጯን)

"…የአይጥ ምስክሯ…

"…ኦቦ ተስፋዬ ይሄ አምቡላ መጋፊያ አረቄ ቤት አይደለም። እንከባበር። ይሄ የጋራ ሃይማኖታችን የከበረ የቅድስና ሥነ ሥርዓት የሚፈጸምበት ሃይማኖታዊ ጉዳይ ነው። ተጣድፎ ምስክርነትህን እዚያው በጃምቦ ቤት አድርገው። ምዕራብ አሩሲ አለፈላት ይላል እንዴ ደግሞ እንዲያውም ጉድ ፈላባት በል እንጂ አባው።

"…በዚህ የማይረባ የጎጥ ኔትወርክ ውስጥ ያላችሁ በሙሉ በሙሉ ከሀ እስከ ፐ የቅርብ ሰዎቼንም ሆነ የሩቅ ወዳጆቼን በሙሉ በአስቸኳይ አቁሙ። እኔ ዘመዴ አልፋታችሁም። ሸዋን በዚህ መልክ አትጠቅሙትም። ሸዋም በዚህ መልክ አይከብርም። ሌሎች ሰዎች ጠፍተው ነው…?

"…ምንአልባትም የማከብርዎት አረጋዊው ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስም በዚህ ጉዳይ ቢተዉ ነው የሚሻለው። ኧረ ደስ አይልም በማርያም። ገና ለገና… ብቻ ደስ አይልም። በቃ መጠጡ ነው ችግሩ እሱን እንዲተው እንመክረዋልን ይለኛል እንዴ በማርያም። አዛረ ምን ጉድ ነው።

"…ደጀኔ ቶላም በማኅበራዊ ሚድያው ላይ የማኅበረ ቅዱሳን አንዳንድ የሸዋ ጎጠኞች፣ እንደ ተስፋዬ ሞሲሳ ዓይነት የአምቡላ ጋን ስር ሰባኪዎች በየፌስቡኩ ስለመሰከሩ፣ ስለተጯጯሁልህ እንዳትኮፈስ። አይገባኝም አይሆንም በል። ይሄን ስታይ ቢያንስ የቀሲስ አብርሃምስ እህት ምን ትላለች አይባልም እንዴ…?  ቀሲስ በላይ መኮንንም እኮ የ3 ልጆች አባት ነው። እንዲያ ከሆነ እሱስ የማይሾም ለምንድነው…?

• አባ ሩፋኤል
• አባ ሕርያቆስ
• አባ ሳዊሮስ
• እና ሌሎችም በዚህ ጉዳይ ላይ ወጥራችሁ ከሸዋ ጳጳስ መብዛት አለበት ብላችሁ የተሳተፋችሁ በሙሉ በየሄዳችሁበት አንገታችሁን ከመድፋታችሁ በፊት በቶሎ ነገርየውን አስተካክሉ። ሌሎቹም ላይ እንዲሁ እቀጥላለሁ።

• ወይ ምስክርነት መች በፍሬንድስነት ሆነና…? ሃኣ…!