2022-01-18 22:48:56
በመቀጠል ከ1426-1460 ዓ.ም ለ34 ዓመት ኢትዮጵያን በመሩት በታላቁ ንጉሥ በዐጼ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥትም ንጉሡ ከሊቃውንት ጋር በመወያየት የበዐሉን ታሪክ ተከትሎ ታቦታቱ ጥር 10 ከመንበረ ክብራቸው ተነሥተው ወደ ባሕረ ጥምቀት
እንዲወርዱና ጥር 11 እንዲመለሱ ተወሰነ።
@zemariian
ታቦተ ጽዮን በሄደችበት ሁሉ በረከትን ትሰጥ እንደነበር የአቢዳራን ቤት በበረከት እንደሞላች፤ የዮርዳኖስን ባህር እንደከፈለች፣ የኢያሪኮን ቅጽር እንዳፈረሰች፣ የፍልስጤማውያን ጣዖት ዳጎንን ቀጥቅጣ እንዳጠፋች ሀገሪቱ ትባረክ ዘንድ ርኲሳን መናፍስት ይርቁ ዘንድ ምድሪቱ በቃል ኪዳኑ ታቦታት ትቀደስ ዘንድ ታቦታቱ በመጡበት መንገድ እንዳይመለሱ ታላቅ ዐዋጅ አሳውጀው በዐዋጁ መሠረት ዛሬ ድረስ በደመቀ መልኩ በዓሉ እየተከበረ ይገኛል፡፡
ከባሕር ማዶ ሰዎች ውስጥ ቼሩሊ በዐጼ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን ቁመቱ 14 ወርዱ 8 ክንድ የኾነ ባሕረ ጥምቀት እንደተዘጋጀ ሲጽፍ፤ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዐጼ ልብነ ድንግል በተገኙበት እጅግ ታላቅ ድንኳን በባሕረ ጥምቀቱ ዙሪያ እንዴት ተተክሎ እንደተከበረ ፍራንቺስኮ አልቫሬዝ ሲጽፍ፤ በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረውን ደግሞ ፔድሮ ፔየዝ ዘግቦት ነበር።
@zemariian
አሁን ባለንበት ጊዜም ዳዊት በመዝ 44፡16 ላይ “በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ” በማለት እንደተናገረ ከመቼውም በበለጠ እግዚአብሔር የወጣቱን ልብ በረድኤት ጎብኝቶት ለቃል ኪዳኑ ታቦታት ክብር አካባቢውን እያስዋበ፣ ታቦታቱ የሚሄዱበትን መንገድ እየጠረገ፤ ታላላቅ ምንጣፎችን ታቦታቱ በሚሄዱበት መንገድ እያነጠፈ ለቃል ኪዳኑ ታቦት እንደ ነቢዩ ዳዊት ከፍተኛ ክብር በመስጠት እግዚአብሔርን እያገለገለ ይገኛል (1ኛ ነገሥት 6፡1-23)፡፡
“የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦትና ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ፥ ከሰፈራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት” (ኢያ 3፡3)
መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
ትምህርተ ሐይማኖት መጽሐፍ ደሞ ትንሽ ይለናል ከላይ የዘረዘርናቸውን ምሳሌነታቸውን #በጥቂቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ባህረ ዮርዳኖስ በ ቅዱስ ዮሐንስ እጅ የተጠመቀበት እና ጥምቀትን የመሰረት ምስጢር ነው
ኢየሱስ ክርስቶስ #ለምን #ተጠመቀ?
@zemariian
ኢየሱስ ክርስቶ የተጠመቀበት ዋናው ምክንያት ዳቢሎስ በ ዮርዳኖስ የቀበረውን የ እዳ በደል ደብዳቤ ለመደምሰስ ነው ደብዳቤውም የሚለው "አዳም የ ዳቢሎስ ወንድ ባርያ ነው ሔዋን የዳቢሎስ ሴት ባርያ ናት "የሚል ነበር ይህ ደብዳቤ እየሱስ ክርስቶስ በ ተጠመቀ ግዜ አጠፋው ።
የኢየሱስ በዮሐንስ መጠመቅ ለ ሁለቱም ክብር ነበር ለዮሐንስ ጌታውን ማጥመቁ
ለኢየሱስ ደግሞ በባርያው እጅ መጠመቁ ትህትናውን እንዲወራ ያደርገዋልና እየሱስም ዮሐንስ የ እግዚአብሔር አብ የባህሪ ልጅ የመንፈስ ቅድስ ቃል አንተ ነህ እያልክ አጥምቅፕኝ ባለው መሰረት እንደተባለው እጠመቀው
ዮርዳኖስ ከላይ አንድ ሆኖ መሀል ላይ ይክፈላል ደግም ዝቅ ብሎ ይገናኛል።
ከላይ አንድ መሆኑ የ አዳምና ሔዋን ልጆች መሆናችንን መከፈሉ ደግሞ የኦሪትና የወንጌል ምሳል ነው ጌታ የተጠመቀው በሚገናኝበት ነው ይህ ሚስጢሩ ኦርትን እና ወንጌልን አንድ ማድረጉ ሰውን ከመላህክት ጋር ማስታረቁን ነው።
@zemariian
#የጥምቀት_ምስጢራዊ_ምሳሌ፦
የ ኖህ መርከብ ዘፍ 7÷17 ወደ መርከቧ የገቡት ሁሉ እንደዳኑ ወደ ጥምቀት የገቡ ሁሉ ይድናሉ ያልገብ ግን ይሞታሉ።
የ አብርሃም ግዝረት ዘፍ 17÷9
ክርስቲያን ለመባል በ ብሉይ ኪዳን መገረዝ እንደሚያስፈልግ ሁሉ በ ሐዲስ ኪዳንም ክርስቲያን ለመባል መጠመቅ አለብን
የ እስራኤል ኤርትራ ባህርን መሻገር ዘፍ 14÷21 ሙሴ የኢየሱስ ምሳሌ በትሩ የመስቀል ምሳሌ ባህሩ የጥምቀት ምሳሌ እዝብ የ ህዝበ እስራኤል ምሳሌ ይሆናል ለምን እኛ በ 40 እና 80 ቀን እንጠመቃለን?
@zemariian
በ ኢትዮጱያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ወንድ በ 40 ቀኑ ሴት ደግሞ በ 80 ቀኗ ታጠምቃለች ይህም የሆነው አዳም በተፈጠረ በ 40 ቀኑ ገነት ሲገባ ሔዋን ደግሞ በ 80 ቀኗ ነው ወደ ገነት የገባችሁ ።
ኩፋሌ 4÷9
ጥምቀት በ ሦስት መንገድ ሊፈፀም ይችላል ይህም •የመንፈስ ጥምቀት ይህ በ ሰው ሳይሆን በመንፈስ የሚደረግ ጥምቀት ነው ልክ እንደ ሐዎርያት ጥምቀት 1ቆሮ 12÷13
• የ ውሃ ጥምቀት ይህ ደግሞ በካህናት አማካኝነት የሚፈፀም ነው ማቴ 3÷13
• የ ደም ጥምቀት። ይህ ጥምቀት የ ሰማህታት ጥምቀት ነው ማቴ 20÷22
በስተመጨረሻ ጥምቀት ለምን በውሃ ሆነ???
ጥምቀት በውሃ ለምን ሆነ እየሱስ ክርስቶስ ለምን በውሃ ተጠመቀ ባለፀጋ ነው ለምን በወተት ወይም በማር አልተጠመቀም ?
ምክንያቱም በውሃ የተጠመቀበት
በኖህ ዘመን የሰው ልጅ በውሃ ጠፍቶ ነበር በግብፃዉያን በባህር ሰምጠው ነበር ሰለዚህ ውሃ ለመሀት ብቻ ሳይሆን ለምህረትም እንደሚሆን ለማስረዳት ነው
ማርና ወተት ሌላም በባል ፀጋ ቤት ነው የሚገኘው ውሃ ግን በ ሁሉም ቤት ስለሚገም ነው
በውሃ ካልታጠብን እንደማንነፃ እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ከ ስጋና ነፍስ እድፍ ትጠራላችሁ ሲል ሲያመላክት ነው
ውሃ መልክን እንደሚያሳይ እናንተም ብትጠመቁ ስላሴን ታያላችሁ ሲል ነው።
ት/ት ሐይማኖት መጽሐፍ
#3 ከተራ ምንድን ነው?
ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡
በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰቡ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥሉ ይውላሉ፡፡ የምንጮች ውኃ እንዲጠራቀም ይከተራሉ (ይገድባሉ) ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ (ለጥር 11) ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡
@zemariian
በተጨማሪ በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማህሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ።
በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ በዋዜማው የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፣ ምሳሌ ሲሆኑ ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡ መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌ።
@zemariian
‹‹ቃና ዘገሊላ›› ምንድነው?
ቃና ዘገሊላ በቀጥታ ትርጉም የገሊላዋ ቃና ማለት ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አስተምህሮ በጥምቀት በዓል ማግስት(ጥር 12) ቀን የቃና ዘገሊላ በዓል ይከበራል፡፡ ይህ በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ በድምቀት የሚከበር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዳራ ያለው በዓል ነው፡፡ በዓሉ ቃና ዘገሊላ የሚል ስያሜ ያገኘው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ሀገር ክፍል በምትሆን ቃና በተባለችው ቦታ በፈፀመው ተአምር መነሻነት ነው፡፡
8.3K views19:48