የባከነች_ነብስ #እውነተኛ ታሪክ #ክፍል1⃣ የቤዛዊት አለሙ እዉነተኛ ታሪክ በቀጣዩ ክፋል ያልቃል Plzzz Like ... እንግዳ ከሌለበት ሱቅ ዉስጥ አቤል ለብቻዉን ቁጭ ብሎ አገኘሁት። ገና ሲያየኝ ፊቱ ላይ የሚታየዉ ንቀትና ትዕቢት የንዴቴን መጠን በእጥፍ ቢጨምረዉም አራሴን አረጋግቼ በእናቴ ሞት ምክንያት ወደ ጅማ ሄጄ እንደነበረ አሁን ሙሉ ገንዘቡን ልከፍለዉ እንደምችልና በምትኩ እሱ ጋር ያለኝን ፎቶና ቪዲዮ እንዲያጠፋዉ ጠየኩት። እየሩስ ወደ ሱቅ ዉስጥ መግባት ስላልፈለገች ከዉጭ ቆማ እኔና አቤልን የምናደርገዉን እንቅስቃሴ ትከታተላለች። አለኝ ዉስጤ ያለዉ የጥላቻና የበቀል ስሜት አንጀቴ ሲያላዉሰዉ ይታወቀኛል ብለዉ ዉስጤ ያለዉ ህመም በትንሹም ቢሆን እርጋታ እንደሚያገኝ ባዉቅም ቸኩዬ ነገሮችን ማበላሸት ስላልፈለኩ አልኩት! በእናቴ ሞት የተሰማኝ ሀዘን ላይ ሲያንጓጥጥ መመልከቱ ከሞትም በላይ ሞት ቢሆንም ያለኝ ብቸኛ አማራጭ ትዕግስት ስለነበረ የሚናገራቸዉን ንግግሮች እየመረረኝም ቢሆን መዋጥ ግዴታ ሆነብኝ። በግምት በእድሜ አቻ ልትሆነኝ የምትችል ጠቆር ብላ የደስ ደስ ያላት ወጣት ሴት ወደ ሱቁ ገብታ በፓስታ የታሸገ ነገር አቀበለችዉ አቤል ደግሞ በምትኩ የሚሞሪ ካርድ ሲሰጣት ተመለከትኩ! ፊቷ ላይ ይታይ የነበረዉ ሀዘንና ተስፋ መቁረጥ እሷም እንደኔ የጥቃቱ ሰለባ ስለመሆኗ ምስክር ነበር። አልኩኝ በዉስጤ! ለሴት ልጅ ህመምና ሀዘን እየሰጠ በምትኩ ገንዘብ እየተቀበለ የሚኖረዉ እስከመች ነዉ? ብሎ አሰናበተኝ! ከእየሩስ ጋር ተያይዘን ወደ ቤት ተመለስን አክስቴ ፈቃደኛ ባትሆንም በብዙ ልመናና ለቅሶ ከጅማ ሽጬ ከመጣሁት ገንዘብ ላይ የተወሰነዉ በእናቴ ስም የሚጠራና በአክስቴ ባለቤትነት የሚተዳደር ሆቴል አዲስ አበባ ዉስጥ እንድትከፍት አስማምቼያት የተቀረዉን ገንዘብ የእናቴ የዘወትር ህልም የሆነዉና ሳትፈፅመዉ ሞት የቀደማት የእርዳታ ድርጅት መክፈት በእኔ አቅም የማይቻል ስለሆነዉ ገንዘቡን ለእርዳታ ድርጅት ለመስጠት መወሰኔን ገለፅኩላት! አክስቴ እንደማይገባት አዉቃለሁ ሊገባትም አይችልም እኔ ግን ነግቶ ነገ ላይ ለመቆም ልቤ ቆሟል ሁሉም ነገር ፍፃሜዉን ሊያገኝ አንድ ምሽት ብቻ ፊት ለፊቴ ተደንቅሯል እንዳረጀ ዉሻ ሂድ ብሎ ይህንን ምሽት በካልቾ መቶ የሚያባርርልኝ ማን ይሆን? ማንም! ... ............. ይቀጥላል.......... plzzz 60 Like ቀጣዩን#ክፍል እንዲቀጥል ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ አሰተያየት ካላችሁ @Abusmovies አድርሱን Join&share @Zeget77 ማንበብ ባህላችን ይሁን 358 views , 06:59