Get Mystery Box with random crypto!

የጥያቄ መልስ 'ራዕይ ዮሐንስ'22-18 እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን 81 | ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ

የጥያቄ መልስ "ራዕይ ዮሐንስ"22-18



እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን 81 መጽሐፍ ቅዱስ ሳታጎል ትቀበላለች ነገር ግን ሌሎች ዘመን አመጣሽ ቤተ እምነቶች 61 ነው ምንቀበለው ብለው ያስተምራሉ ለዚህ አስተምሕሮታቸው እንደ ማስረጃ አድርገው የሚያቀርቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ( ራእ 22-18) " ማንም በዚህ ላይ አንዳች ቢጨምር እግዚአብሔር በዚሕ መፃሕፍ ላይ የተፃፍትን መቅሰፍቶች ይጨምርበታል ። ማንም በዚህ በትንቢት መጽሐፍ ከተፃፍት ቃሎች አንዳችን ቢያጎድል በዚሕ መፃፍ ከተፃፍት ከሕይወት ዛፍ እና ከቅድስቲቱ ከተማ እግዚአብሔር እድሉን ያጎልበታል " ሚለው ቃል በመጥቀስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጨምራለች ብለው ይሞግታሉ ። ነገር ግን ይሕን አባባል በጥሞና ስናጤ ነው የዮሐንስ ራዕይን ብቻ የሚመለከት እንጂ ሌሎቹን የማይመለከት ሆኖ እናገኘዋለን ። "በዚህ በትንቢት መፅሐፍ " አለ እንጂ ከዚሕ መጽሐፍ ቅዱስ ውጪ አላለም ። ይሕም ሚያሳየን የተጠቀሰው ምዕራፍ የዮሐንስ ራዕይን ብቻ ሚመለከት መሆኑን ነው ። መጽሐፍ ቅዱስም እንዲሁ አንድ ላይ ተጠረዞ ሆኖ የተገኘ ሳይሆን በተለያየ ዘመናት በተላያየ ግዜ የተፃፍ ናቸው ። ፀሐፊዎቹም የተለያዩ ናቸው እንጂ አንድ ሰው አንድ ግዜ ሁሉኑም የፃፍቸው አይደለም ።

ይህ ቃል የተጠቀሰበት የራሱ የሆነ ምክንያት አለው ክርስቲያኖች ክርስትናን ያስፍፋት በቀላል እንዳልነበር ከማናችንም የተሰወረ አይደለም ። [በተለይ የሮም ቤተክርሰቲያን በክርስትያኖች ላይ ያልመዘዙት ሰይፍ ። ያላሳረፍት የመከራ ዱላ አልነበረም ። በዘመነ ሰማእታት ክርስቲያኖች እንደሽንኩርት ሲቀረደዱ ቅዱሳት መጻሕፍትም የእሳት አዱኛ ሆነው ነበር ። ክርስትያኖች መከራውን አሳልፈው በእግዚአብሔር ሐይል ሰላም በሆነበት ግዚ ከቅዱሳት መጽሐፍ ሁሉም ሲገኙ የዮሐንስ ራዕይ ግን ይጠፍል ። በዚህም አዝነው ሳለ የዮሐንስ አፈወርቅ በግዞት ሳለ ግዚ ስለዚህ መጽሐፍ መቃጠል ያዝን ነበርና መጽሐፍ ቅዱሱን ዮሐንስ ሐዋርያ ፍጥሞ በተባለች ደሴት ያየውን አንድም ሳያስቀር እግዚአብሐር ገልጦለት ፅፎታል ። በዚህም በመዝጊያው ላይ መሳጠንቀቂያ አሰፈረበት ። (ዮሐንስ ሐዋርያ የያውን ሁሉንም እግዚአብሔር ገልጦልኝ ፃፍኩት ያጎደልኩትም የቀነስኩትም የለም ሲል )ሌሎች እንዳይጨምሩም እንዳይቀንሱም ይህን ቃል ጠቅሷል

ዲያቆን ፍፁም ከበደ



https://t.me/ZDfitsumkebede
https://t.me/ZDfitsumkebede