Get Mystery Box with random crypto!

'ዱባ እና ትውልዱ' ዱባ፦ በቤተክርስትያንናችን አስተምህሮ ከቤተክርስትያን ቅጥር ውስጥ እንዲገባ | ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ

"ዱባ እና ትውልዱ"

ዱባ፦ በቤተክርስትያንናችን አስተምህሮ ከቤተክርስትያን ቅጥር ውስጥ እንዲገባ አይፈቀድም ብለው ሲያስተምሩ ከአውደምሕረቱ ሚስጥሩን ለማወቅ ጓጉቼ እጠብቅ ይዣለው ዱባ ደግሞ ከምግብነት ባለፈ ትርጉም ይኖረው ይሆን!! በእርግጥ የኔ አለማወቅም ገና ብዙ ትምህርት ንባብ እንደሚያስፈልገው ትዝብት ጥሎልኝም አልፏል መለስ ከማለቴ እንዲህ እያሉ ሊያመሰጥሩ መደንርደሪያ ይዘሩ በትዝብት ጀምረዋል አንዳንዴ ከቤተክርስቲያን ዱባና ቅል ሲገባ ሳይ ይገርመኛል በተለይ የከተማ ደብራት ላይ ይስተዋላሉ ይህ አለማወቅ ነው አሉ ጮክ ብለው ቁጣም ምክርም አዘል በሆነ ቃል ። ዱባ ወጨው ብዙ ነው ሚጣለው ከውስጥ ማለት ነው ። ትውልዱና ዱባው ተመሳስለውብኛል ያው ናቸው ሚጣል ነገር ውስጣቸው በብዛት ከመብዛቱ የተነሳ ። ትውልዱ ክፍቱ ተጣይ ነው ፤ ለተፈጠረለት ሰዋዊ ማንነት መቆም ያልቻለ ትውልድ ተጣይ ነው ። ብቻ አደር ባይነቱ በሰፍው ምድር ላይ ምድሩ ሳይሆን እሱ አስተሳሰቡ ጠቦ መገኘቱ ተጣይ ነው ፤ ተነካው እንጂ ነካውብሎ አምኖ መቀበል የጎደለው ጉድለቱን ሚነገረው ሳይሆን ያልሆነውን ነህ እያለ ሚሞላው መፈለግ መሻቱ ሁሉ ተጣይ ነው። ሁለት ጆሮ ቢኖር አንዱ እራስ ማዳመጫ አንዱ የሌላውን ማዳመጫ መሆኑን መርሳት የቻለ ትውልድ ተጣይ ነው። ከዚህ አመለካከት እንወጣ ዘንድ ምክሬ ነው ጨረስኩ ።


ዲያቆን ፍፁም ከበደ

https://t.me/ZDfitsumkebede።
https://t.me/ZDfitsumkebede።