2022-08-25 01:03:54
ተመድ በአሸባሪው ህወሃት 570 ሺህ ሊትር ነዳጅ እንደተዘረፈ ገለጸ
ነሐሴ 18 ቀን 2014 (ኢዜአ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) በአሸባሪው ህወሃት 570 ሺህ ሊትር ነዳጅ እንደተዘረፈ ገለጸ።
የተመድ ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬስ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች በዛሬ መግለጫውቸው እንዳረጋገጡት በመቀሌ ከሚገኘው የአለም የምግብ ድርጅት ዛሬ ማለዳ ላይ 12 የነዳጅ ታንከሮች ከ570 ሺህ ሊትር ነዳጅ ጋር በአሸባሪው ህወሃት ተዘርፈው ተወስደዋል።
ነዳጁ በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ ለማሰራጨት አገልግሎት ላይ የሚውል እንደነበርም ጠቅሰዋል።
66 viewsAseged, 22:03