2022-07-23 15:10:57
ዑመር ገነቴ ከዑመር ይማም በምንድነው የሚለየው?
~~~
1- ሁለቱም አሕባሾች ናቸው።
አሕባ - ሽ እዚህ እንዲደርስ ያመቻቸው ከዑመር ይማም ይልቅ ዑመር ገነቴ ነው። አሕባ/ሽ ገና በሁለት እግሩ ሳይቆም በ90ዎቹ ከሊባኖስ በመጡ አሕባ/ሾች የማጥመቅ ስልጠና ሲሰጥ መርቆ የከፈተው ዑመር ገነቴ ነው። አሕ/ባሽ እግሩን በተከለበት ከ1992 እስከ 2000 ድረስ የዑለማእ ምክር ቤት ሊቀመንበር ነበር። ከሚያዚያ 2001 ጀምሮ እስከ 2005 ድረስ ከፌደራል መጅሊስ አመራሮች ውስጥ ነበር። ይሄ ዘመን የአሕባሽ ፈተና የጠነከረበት ጊዜ ነው። ሐምሌ 9 እና 10/2004 ራስ ሆቴል ውስጥ በተካሄደ የአሕ/ባሽ ኮንፈረንስ ከ100 የሚበልጡ ሱፍዮች ከመላው ሃገሪቱ ተሰብስበው "ወሃ-ቢዮች" የሚሏቸውን ሙስሊሞች ሁሉ ከኢስላም በማስወጣት የክህደት ብይን ሰጥተው መግለጫ አውጥተዋል። ከ 2005 ጀምሮ ደግሞ እስከ 2010 ድረስ የፌደራል መጅሊስ የጠቅላላ ጉባኤው አባል፣ የመስጂድና አውቃፍ ዘርፍ ሀላፊ እንዲሁም የዑለማ ምክር ቤት አባል ሆኖ ሰርቷል። በዚህም ዘመን በአሕ-ባሾች ምን እንደ ደረሰ የምናውቀው ነው።
2- ሁለቱም ሙስሊሞችን ያ - ከ * ፍ - ራ - ሉ።
አዎ ሁለቱም አላህ ከዐርሹ በላይ ነው የሚሉ ሙስሊሞችን በሀሰት "ሙጀሲማ" የሚል ቅፅል ለጥፈው በከሃዲነት የሚፈርጁ ናቸው። የዑመር ይማም አያከራክርም። "ወሃ-ቢዮች ያረዱት አይበላም፣ ኒካሕ የላቸውም" እያለ ባደባባይ የሚናገር ነው። "ዶክተር" አቡበክር የሚባለውም አሕ-ባሽ በቅርቡ ሆሳእና ላይ ተመሳሳይ ነገር ተናግሯል። እነዚህ ሰዎች የ"ሙፍቲው" ጀማዐ እንደሆኑ የሚታወቅ ነው። ዑመር ገነቴ እራሱ "አላህ ከ0ርሽ በላይ ነው" የሚሉ ሙስሊሞችን ከኢስላም የሚያስወጣ ፅንፈኛ እንደሆነ የድምፅ ማስረጃ አለ።
3- ሁለቱም ሙስሊሞችን በጠላት ለማስመታት የሚጥሩ ጠላቶች ናቸው።
ዑመር ገነቴ አይደለም እንዴ ክርስቲያኖችን ጭምር ለአመፅ የጠራው? ወደ ደም መፋሰስ የቀሰቀሰው? መስጂድ እያቃጠለ፣ ሙስሊሞችን እየገደለ ያለው ቡድን የሱ ጀማዐ አይደለምን? እስኪ መቼ ነው የሙስሊሞች መሪ፣ የዑለማእ ቁንጮ ነኝ የሚለው ይሄ ሰውዬ በተከታዮቹ የተፈፀመውን ይህንን ፀያፍ ድርጊት የኮነነው? እንዲያውም ቅስቀሳ ሲያደርግ ነው የምናውቀው። እንዲያውም ሙስሊሞችን በጠላት ለማስመታት በግላጭ ሲሰራ የኖረ ሰው ነው። እስኪ ይህንን ጥቅምት 30/2012 በሸገር ሬዲዮ ከቀረበው የዑመር ገነቴ ቃለ ምልልስ የተወሰደ ንግግር መላልሳችሁ አስተውሉ!! ይሄው:–
"ለባለስልጣኖቹም፣ ለእነ አባይ ፀሃዬ – የዚያን ግዜ የደህንነት ኃላፊ ነበሩ –
‘ተው እባካችሁ! ይኼ ችግር (#ሰለፍያን ማለቱ ነው) መንግስት ላይ ይወጣል። እኛ ላይ ብቻ ሳይሆን እናንተም ላይ ይደርሳል’ እላቸው ነበር።
በኋላ እንግዲህ በእነመለስ ግዜ እነርሱ ላይ ሲደርስ መጥፋት አለበት ብሎ ያ ሁሉ ችግር ተፈጠረ። መጀመሪያውኑ ከውጥኑ ማጥፋት ይቻል ነበር።"
•
ተመልከቱ! መንግስት ሳያስብ በፊት አሕባሽ ያልሆኑ ሙስሊሞችን እንዲያጠፋላቸው ሲወተውት ነበር ማለት ነው። እነዚህ አቅሙ ቢኖራቸው እንደ ዮሐንስ ሙስሊሞችን አጋድመው ያርዱ።
ቀጠለ:—
"መንግስት የዚያን ግዜ በጎናችን አልቆመም። መፈለግ አይፈልገውም። ሙስሊሙ ላይ ብቻ ይቀር መስሎታል እንጂ ወደ መንግስት ያልፋል አልመሰለውም። አሁን ሀገሩ በሙሉ ተዳርሷል። ለማጥፋት አልተቻለም። ወደአንድነት መጥተን ሰላም ቢሆን ይሻላል ሀገሩ ብለን ነው። ወደን አይደለም በአንድነት የምንታየው። ማጥፋት ካልተቻለ አብሮ በሚሆንበት ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል በሚል ነው።"
•
ምንኛ ልብ የሚያደማ ንግግር ነው?!
4- ዑመር ገነቴ ከዑመር ይማም በላይ የተውሒድ ደዕዋን ሲዋጋ የኖረ ነው። እራሱ እንዲህ ሲል ይመስክራል:-
«ሐጂ ሙሐመድ ሣኒ–ሐጂ ሙሐመድ ሣኒ ትላላችሁ! ሐጂ ሙሐመድ ሣኒ እና ዐብዱ-ር-ረሕማን ናቸው ወሃቢያን የመሰረቱት፡፡ ሐጂ ሙሐመድ ሣኒ እንጂ ዑመር አይደለም ወሃቢያን የመሰረተው፡፡
እኔ ብቻዬን ስታገል ነው የኖርኩት፡፡.....
ዐቂዳ ትላላችሁ ...ሐጂ ሙሐመድ ሣኒ ነው ወሃብያን የመሰረተው። ዐብዱ-ር-ረህማን ነው ወሃብያን የመሰረተው፡፡ ... ወደኛ የመጣችሁ እደሆነ የዘከዘኩት እንደሆነ ሌላ ታመጣላችሁ!……
ወሃብያን የመሰረተው ሐጂ ሙሐመድ ሣኒ እና ዐብዱ-ር-ረህማን ናቸው፡፡ ስንታገል ነው የኖርነው .... ሐጂ ሙሐመድ ሣኒ ናቸው እንዴ ወሃብያን የታገሉት? ማን መሰረተው?"
ዑመር ገነቴ በ 90 ዎቹ መጀመሪያ ላይ ባህርዳር ላይ በፖሊስ በታጀበ ስብሰባ ታዳሚዎችን ሲያስጨንቅ ነበር።
አንገቱን የደፋበትን ፎቶ እየለጠፋችሁ አጉል አንጀት ለመብላት አትሞክሩ። ሓሪሥ አልሙሓሲቢ ከዑመር ገነቴ በዒልምም፣ በአደብም፣ በአቋምም የተሻለ ነበር። ኧረ ጭራሽ የሚነፃፀሩም አይደሉም። ነገር ግን በያዘው የቢድዐ አቋም የተነሳ ዙህዱም፣ አደቡም፣ ... በነ ኢማሙ አሕመድ ከመወገዝ አላዳነውም። "እርጋታውና ልስላሴው አይሸውድህ። እራሱን በመድፋቱ እንዳትሸወድ" ነበር ያሉት። ይሄኛው ምኑ ነው የሚሸውደን? እብሪትና በባዶ መኮፈስ እንጂ ምን አደብ አለውና! ለማይታዘነው እያዘናችሁ ተሸውዳችሁ ሌሎችን አትሸውዱ። ለእዝነትም ቦታ አለው። ያለ ቦታው እያዋላችሁ አታሪክሱት። ለማይገባው እያለቀሳችሁ ቅጥ አታሳጡት። በጥቅም ተጋሪዎቹ ወይም በመዝሀብ ዘመዶቹ ሙሾ አትሸወዱ። ሁለቱም ዑመሮች በዐቂዳም ሆነ ለሙስሊሞች ባላቸው አደጋ ልዩነት የላቸውም።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
273 views12:10