2022-07-13 03:41:19
ቀዝቃዛ በቀል..!
(ይነበብ ደስ የሚል ታሪክ ነው)
የElementary ተማሪ እያለሁ ጊቢ ውስጥ አሉ ከሚባሉ ሰቃዮች ውስጥ ስሜ ይጠራ ነበር አሁን መደነዜን አትዩ! እናላቹ 8ተኛ ክፍል ሳለሁ አንድ ጥላሲስ አስተማሪ የበደለኝን በደልና እንዴት እንደተበቀልኩት ልነግራቹ ነው አመጣጤ።
አማርኛ መምህር ነበር ሰውየው እኔ ደግሞ ጥሎብኝ አማርኛ ትምህርት, ቅኔ, ምሳሌያዊ አነጋገር ቅብርጥሴ በቃ አይመቹኝም ነበር። ይኸው አሁንም ድረስ አማርኛ ሳወራ ቃላት ሚያጥሩኝ ለዛ ነው። እና ሰውየው ለካ ደደብ አርጎ ስሎኛል ሲጠላኝ አልኳቹ፣ ከዛ የሆነ ቀን የቀኑን ትምህርት ቶሎ ጨረሰና ተማሪ እያስነሳ ማዘፈን ጀመረ።
የፈራሁት አልቀረም "ዝፈኚ" ተባልኩ
አልዘፍንም!
"ለምን?"
ሀይማኖቴ ስለማይፈቅድ "
ይሄኮ ትምህርት ቤት እንጂ መስጂድ አይደለም"
የልጅ አእምሮዬ እየደነገጠ ቢሆንም በድፍረት ''ሀይማኖቴ ሚያዘኝን ለመተግበር ቦታ አልመርጥም አልኩት'' ከተቀመጠበት በግልፍት ተነስቶ በጥፊ ፊቴን ፍም አለበሰው፡፡
በህይወቴ ለመጀመሪያም ለመጨረሻም ቀን አስተማሪ የመታኝ የተቆጣኝም የዛኔ ነበር ። ይህ አልበቃ ብሎት "አንቺ ተስፋ ቢስ 87/100 ኮርጀሽ ነው ያመጣሽው" ብሎ 10 ማርክ ጎመደና 1ኛ ምወጣዋን ልጅ 2ተኛ አስወጣኝ
ለህይወት ዘመኑ ሚበቃ እርግማን ነው ቀልቤ የረገመው፡፡
አልሀምዱሊላህ! ዛሬ clinical pharmacy ተምሬ ልመረቅ ቀናት ይቀሩኛል ለpractice የተመደብንበት ሆስፒታል ለድሮ ሰፈራችን ቅርብ ስለሆነ ወደዛ ስሄድ ብዙ ትዝታዎቼ ይቀሰቀሳሉ.. ትምህርት ቤቱን ሳየው ራሱ ትዝ ሚለኝ ያ ከይሲ ሰውዬ ነው።
ያ አረመኔ መምህር ታዲያ መች እለት እኔ የተመደብኩበት ሆስፒታል ድረስ እንደ ደህና ሰው ጎምለል እያለ ቢመጣስ ያ ሁላ ረግሜው እስካሁን አለመሞቱን ሳይ ነው በቃ በእርግማኔ ተስፋ የቆረጥኩት ። መሞት ቀርቶ አላረጀም ሁላ፡፡ ካርዱ ሰተት ብሎ እኔ ያለሁበት ክፍል መጣ። ከSenior ዶክተሩ ጋር ስለህመሙ አውርተው መድሀኒት አዞለት ሲወጣ እኔም ተከትዬው ወጣሁና ጠራሁት። ዛሬ ከትናንቱ ተለውጫለሁና አላወቀኝም ነገሩ ግን "የወጋ ቢረሳ...." ነው፡፡
ነጭ ጋውኔን ለብሼማ እንዴት አያክብረኝ...? "አቤት ዶክተርዬ" አለ ይቅርታ ይህን ስልህ... ነገር ግን ብዙ በህይወት የመኖር ተስፋ የለህምግፋ ቢል 2ወር ነው በህይወት ምትቆየው።አዝናለሁ የካንሰር በሽተኛ ነህ ዶክተሩ ሊነግርህ ስላልቻለ ነው እኔን የላከኝ። ፣ ያዘዝልህም መድሀኒት ማስታገሻ ብቻ ነው ....ብዬ ብበቀለውና ተስፋውን ባጨልምበት ሁሉ የያዝኩበት ቂም አይለቀኝም ነበር ግን ህሊና ሚባል ነገር አለ።
የመድሀኒት ማዘዣውን ረስቶ ስለነበር የወጣው እኔም እሱን ልሰጠው ነው የጠራሁት:: prescriptioኑን ሰጥቼው የቀድሞ መምህሬ እንደነበርና እንደማከብረው ከነገርኩት በኋላ.. "የሰው ልጅ ግን ተስፋ ቢስ ብለህ አትሳደብ!" የሚል አጠር ያለ reminder ሰጥቼው ዞሬ ሳላየው ወደክፍሌ ተመለስኩ በነገራችሁ ላይ ሰውየው ታይፎይድ ነበር ያመመው። በአንድ መርፌ ፀጥ ማረግ ነበር ( ማለቴ ህመሙን!
ውብ የካንፓስ ቆይታ ከዘ ካንፓስ ጋር !
======================
JOIN : @z_campus
JOIN : @z_campus
======================
4.5K viewszoog, edited 00:41