Get Mystery Box with random crypto!

የመስቀሉ ፍቅር ✞

የቴሌግራም ቻናል አርማ ymeskelu_fiker — የመስቀሉ ፍቅር ✞
የቴሌግራም ቻናል አርማ ymeskelu_fiker — የመስቀሉ ፍቅር ✞
የሰርጥ አድራሻ: @ymeskelu_fiker
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.27K
የሰርጥ መግለጫ

✞ የዚህ channel አላማ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮቶችን በማስተማር ፤ በጥልቀት የመስቀሉን ፍቅር ፤የመስቀሉን ውለታ ለአለም መናገር ፤ ለወጣቶች የሚሆን የመስቀሉን ፍቅር የሚያስረዳ ተምርታዊ ጽሁፎችን ማቅረብ እና ወጣቱን ወደ መስቀሉ ፍቅረ ማምጣት ነው፣ አላማችን።
ለሀሰብ ጥያቄ @Metsenanat

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

3

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-17 14:57:04 #ዘመኔን ልስጥህ

በአባትነት ፍቅርህ መለወጥ ፣ በትዕግሥትህ መሰልቸት ፣ በምሕረትህ መታከት ፣ በቸርነትህ መጓተት ከቶ የማይታይብህ ሁሌ አዲስ የሆንኽ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ አመሰግንሃለሁ ። የሆንኩትን ሳታይ የሆንከውን አስበህ በዚህ ቀን ደግሞም ደቂቃ የባረከኝ አንተ ነህ ተመስገን ። ዓለሜ ላየሁት እንጂ ላየኽልኝ አይደለም ። ዘመኔ የቁጥር እንጂ የዕድሜ አይደለም ። ያለአንተ ዘለዓለም የዜሮ ብዚት ነው ። ቀኔን እሰጥህ ዘንድ እርዳኝ ። ጌታ ሆይ ዓለሜ ለአንተ መኖር ነው ። ዘመኔን አደራ ዕልሃለሁ ። ዘመኔ ሚዛን የሚደፋው አንተ ስትደምቅበት ነው ። አዲስነትህ ዘመኔን ያድሰው ። መራመዴ ስፍራን ይለውጣል ። ማራመድህ ግን በሕይወት ያስጌጣል ። ላልከበርክበት ማንነቴ ዕድሜ መለመኔን ይቅር በል ። ለአንተ ያልኖርኩበትን ዘመን ማለቴን ይቅር በል። በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን ስላልጎደለው ምሕረትህ ተመስገን ። ጌታ ሆይ ዘመንህ ዘመኔ ይሁን ። ሰው መሆንህ ሰው ያድርገኝ ። ለአንተ እሺ ለዓለም እቢ ምልበትን ፀጋ ከፀባዖትህ አፍስስልኝ ። ያለ አንተ ሮጥኹ መድረሴ አያረካም ። ያለአንተ ነቃው መንቃቴ አያሻግርም ። ያለ አንተ መርጥኹ ያገኘውት ግን አይፈውስም ። ያለ አንት አሰስኩ ዕድሌ ግን ሸክም ሆነ ። ያለ አንተ ዘመን ቆጠርኩ ዘመኔ ገን ዕድሜ አልሆነም ። ጌታ ሆይ አንተን ተጠግቶ ዓለምን መካድ ግን ሁሉን በሁሉ ማትረፍ ነውና ዘመኔን ዘመንህ ይቀድስ ። ቀኔን መቅደምህ ይባርክ ። ወጣትነቴን ቃልህ ያለምልመው ። እልኸኛውን ልቤን መቻል የደግፈው ። ከሁሉ በላይ ለአንተ ምኖርበት ዘመን ብቻ ዘመን ይሆናል በዚህ ባሪያህን ትባርክ ዘንድ እሻለሁ ። በማላፍርበት ደግነትህ ለዘለዓለሙ አሜን !
1.2K viewsበርናባስ ነኝ, 11:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 06:38:15 "አንባቢ ሆይ"
"እርሱ ብቻ አዳኝ የሆነውን ጌታ ካመንኸው ትድናለህ!"

#አምኖ_የመዳን_ቀን_አሁን_ነው ።

እግዚአብሔር ሰዎችን ሁሉ ከአንድ ሰው እንደ ፈጠረ መጽሐፍ ቅዱስ ይመሰክራል (ዘፍ 1፥26) ፤ (የሐዋ 17፥26)። የሰው ልጅ በሙሉ በቦታና በጊዜ ተወስነዋል። ይህ የሆነበት ምክንያትም በተመደበላቸው ዘመን ሲኖሩ ፣ እግዚአብሔርን ፈልገው የገኙት ዘንድ እርሱን የመመርመር መንገድ እንዲሆንላቸው ነው። መጽሐፍ ፣ “ምናልባትም እየመረመሩ ያገኙት እንደ ሆነ፥ እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ ከአንድ ፈጠረ፥ የተወሰኑትንም ዘመኖችና ለሚኖሩበት ስፍራ ዳርቻ መደበላቸው። ቢሆንም ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም።" — ሐዋ17፥26-27 ይላል።

በዚህ በተመደበልን ዘመን ውስጥ እግዚአብሔር ያለማወቅን ወራት አሳልፎ የንስሓ ዘመንን አምጥቷል ፤ ይህም ንስሓ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ በማመን የኀጢአት ስርየትና የዘለዓለም ሕይወት እንደሚገኝ በየዘመኑ የሚሰበክ እውነት ነው። ሁሉም ሰው የራሱ ዘመንና የመኖሪያ ቦታ ዳርቻ ስለ ተመደበለት ፣ በተመደበለት ቦታና ዘመን የሚሰበከውን የንስሓ ጥሪ አምኖ በመቀበል መዳን የሚችለው ፣ በዚሁ ዘመን በተሰጠው ዕድል ውስጥ ነው።

ይህን ዕድል ሰምተን የመንጠቀምበትን ዘመን መጽሐፍ “... እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።” — 2ኛ ቆሮ 6፥1-2 ይለዋል። ስለዚህ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ይድናል ስንል ፤ በዚህ በተመደበለት ቦታና ጊዜ ሲኖር ፣ እግዚአብሔር ያቀረበለትን የንስሓ ጥሪ ተቀብሎ በወንጌል በማመን የሚድንበት ጊዜም አሁን ነው እያልን ነው። ይህን ማለት ያስፈለገበት ዋና ምክኒያት ፣ ሰው የዳነ መሆኑን ለማወቅ የግድ ዕለተ ሞቱን መጠበቅና ነፍሱ በእግዚአብሔር ፊት ቀርባ የኩነኔን ወይም የመዳን ፍርድን እስከንሰማ ድርስ ፣ ለመዳናችን እርግጠኛ መሆን የምንችልበት ነገር የለም የሚሉ ብዙ ሰዎች ስላሉ ነው።

የዮሐንስ ወንጌል ይህን እውነት ሲመሰክር ፣ “በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል።” — ዮሐ 3፥18 ይላል። የእግዚአብሔር ቃል የታመነ ነው።

የተወደደውን ሰዓት አሳልፎ ፣ የመዳን ቀንን አባክኖ ፣ የወንጌልን ቃል መስማት አልፈልግም ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ አላምንም ፣ ከኀጢአቴም ለመዳን በንስሓ ወደ እግዚአብሔር አልቀርብም ብሎ የሞት ሰው ከሞት በኋላ የመዳን ተስፋ ሊያገኝ አይችልም ፤ (ዕብ 9፥ 27፥28) በሕይወት እያለ በወንጌል አምኖ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ የዳነ ሰውም ወደ እግዚአብሔር ሲሄድ ፣ እግዚአብሔር በወንጌል የተናገረውን ቃሉን ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ የገለጠውን ፍቃዱን ፣ በክርስቶስም የሰጠውን የመዳን ተስፋም ለውጦ በልጁ ያመኑትን አላውቃችሁም ይል ዘንድ የሚችል አምላክ አይደለም። የመዳን ቀን አሁን ነውና በዚህ ሕይወት እያለን በወንጌል እንመን። የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ አምነን በንስሓ ወደ እግዚአብሔር አሁኑኑ እንቅረብ ፣ መዳን በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኝ የእግዚአብሔር ጸጋ ነውና። ተባረኩ

ታናሻቹ.....!!!

@ymeskelu_fiker
1.3K viewsበርናባስ ነኝ, edited  03:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-11 01:10:26
1.3K viewsበርናባስ ነኝ, 22:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 22:11:37 እግዚአብሔር ታሪክህን ይለውጣል


   " የሰደድሁባችሁ ታላቁ ሠራዊቴ አንበጣና ደጎብያ ኩብኩባና ተምች የበላቸውን ዓመታት እመልስላችኋለሁ።  ብዙ መብል ትበላላችሁ፥ ትጠግቡማላችሁ፤ ከእናንተም ጋር ተአምራትን የሠራውን የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ስም ታመሰግናላችሁ፤ ሕዝቤም ለዘላለም አያፍርም።"
ትንቢተ ኢዮኤል 2 : 25-26

       ቢራቢሮን የሚጠላና የሚፀየፍ ይኖር ይሆን?
አባ ጨጓሬንስ የሚወድ ይገኝ ይሆን?

      ቢራቢሮ አባ ጨጓሬ እሆናለሁ ብላ አስባ አታውቅም። ትላንትናዋ ( የአባ ጨጓሬ) ማንነቷ የተጠላ፤ የተናቀ፤ በምድር የምትርመሰመስ፤ ያያት የሚገድላት ነበረች። አሳዳጆቿ ነገዋን ቢያስቡም በዛሬው ማንነቷ ሊወዷት አይችሉም።

      ለሁሉም ጊዜ አለው ነውና ቃሉ አባ ጨጓሬው ቢራቢሮ ማንነቱን ሲላበስ ትላንት ያሳደደው ሁሉ ዛሬ ሊይዘው ይፈልጋል፤ ሊያየው የማይፈልገው ሁሉ በእጁ ሊጨብጠው ይሻል፤ በምድር ከመርመስመስ ተላቃ ግራቪቲ ሳይዛት ትበራለች።

       ወዳጄ ዛሬም ያንተ ህይወት እንደ አባጨጓሬው በሰው የመጠላት፤ በመሰደድ፤ በመገደል፤ በመናቅ፤ እንደ እርኩስ በመቆጠር ህይወት ውስጥ እያለፍክ ይሆናል። እውነት እልሀለው እግዚአብሔር በመለኮታዊ ማንነቱ ባንተ ህይወት መሀል ጣልቃ ይገባል። የዛሬ መናቅህን ያያል፤ በሰው መጠላትህን ይመለከታል፤ አንገት መድፋትህን ያስተውላል፤ መገለልህ ግድ ይለዋልና ወደ ቤትህ ወደ ህይወትህ ጎራ ይላል።

ይህ ማንነትህ የዛሬው አይቀጥልም። የጠሉህ እስኪወዱህ ድረስ ይፈልጉሀል፤ በገደልነው የሚሉህ በተንከባከብነው ይሉሀል፤ አንገት መድፋትህ ታሪክ ሆኖ ክንፍ አውጥተህ ትበራለህ፤ አሳዳጅህ ሁሉ በቤቱ የሚጋብዝህ ይሆናል።

      እግዚአብሔር የጉብኝት ወቅት አለው። በውርደት ጀምረህ በውርደት አትፈፅምም በክብር እንጂ፤ በስቃይ ጀምረህ በጣር አትደመድምም በደስታ እንጂ፤ በሀጢአት ጀምረህ ነበር በርኩሰት አትጨርስም ክርስቶስን በማመንህ በትንሳኤና በህይወት ትደመድማለህ።

     ዛሬ ሁሉም እየተፈራረመብህ ነው፤ እያደመብህ ነው ግን እግዚአብሔር ድምፅን በድምፅ የሚሽር አምላክ ነውና የጠላትህን ምክር ገልብጦ ለትንሳኤ ያቆምሀል። በጠላትህ ፊት ይባርክሀል።

      በወጀብ በማዕበሉ በእግዚአብሔር መታመንህን አትርሳ። ከፍ የሚያደርግህ እግዚአብሔር ነው።
1.4K viewsበርናባስ ነኝ, 19:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-07 08:06:37
1.3K viewsበርናባስ ነኝ, 05:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 17:41:27 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

"ናና ሙሽራዬ"

የደስታ አለም በናፍቆት የሚጠበቅ ፣ የበረከት ምድር ለመውረስ የሚየጓጓ (ነገር ገን በእምነት የተወረሰ)፣ አዲስ ህይወት ፣ አዲስ አለም ያልታየ የልተስማ ፣ የሚታይ የሚሰማ ፤ የብቸኝነት ጉዞ መቋጫ ፣ የንግስና ፣ የክብር ፣ የድምቀት ቀን ፤ የሙሽሪት የሰረጓ አለት ነው። የሙሽሪት ተስፋዋ ፣ ደስታዋ ፣ ክብራ ፣ ጌጧ ፣ እና ኩራቷ እለፎም ሁለንተናዋ ሙሽራዋ ነው። ሙሽሪት በሰረጓ እለት ሙሽራዋ ባይገኝ ወይም ባይኖር የሙሽሪት ሰረግ ወይም ያ የደስታዋ ቀን በቅጽበት ወደ ቅሶ ወይም ወደ ሃዘን ይለወጣል። ይመጣል ፣ መቶም ይወስደኛል ብላ ተውባና አጊጣ የጠበቀቺው ሙሽራዋ ቢቀር ህልሟ ቅዠት ፣ ክብሯ ውረደት ፣ ጌጧ ከንቱ መና ነው የሚሆንባት። የትኛዋም ሙሽሪት ምሽራ የምትሆነው የሚያገበት ፣ የሚወስዳት ድክመትሽ ድክመቴ ፣ የኔ ነገር ያንቺ ፣ ያነቺ ነገር የኔ ብሎ ሊወስዳት የሚመጣ ሙሽራ ሲኖር ነው።

ወንጌል እንዲ ይላል ፦ “ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው፤ ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል።..." ዮሐ 3፥29

“ሰባቱም ኋለኛዎች መቅሠፍቶች የሞሉባቸውን ሰባቱን ጽዋዎች ከያዙት ከሰባቱ መላእክት አንዱ መጥቶ፦ ወደዚህ ና፥ የበጉንም ሚስት ሙሽራይቱን አሳይሃለሁ ብሎ ተናገረኝ።” ራእይ 21፥9

“የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ ሚስቱም ራስዋን ስላዘጋጀች ደስ ይበለን ሐሤትም እናድርግ ክብርንም ለእርሱ እናቅርብ።” ራእይ 19፥7

“መንፈሱና ሙሽራይቱም፦ ና ይላሉ። የሚሰማም፦ ና ይበል። የተጠማም ይምጣ፥ የወደደም የሕይወትን ውኃ እንዲያው ይውሰድ።” ራእይ 22፥17


የሙሽራው መምጣት ሙሽሪትን ወደ ተሻለ ፣ ወደ ላቀ ፣ ወደ ከበረ አዲስ ህይወት ይዟት ለመሔድ ነው። በዚው ልክ የሙሽራችኝ የክርስቶስ መምጣት በስሙ ለምናምን ለኛ ፣ በፍቅሩ ለተማረኩ ሙሽራዎች ሁሉ ደስታ ፣ ሰላም ፣ ህይወት እና ዘላለማዊ እረፍት ነው። የትኛውም ሰው ያለ ሙሽራው ክርስቶስ ባዶ ነው ፣ የትኛውም ተቋም የለ ሙሽራው ኢየሱስ የሞት አውድማ ነው። ሁሉም ነገር ክርስቶስን ሲይዝ ሲደገፈ ነው ገልቶ የሚታየው።

አጭር መልእክት

ወዳጄ መጽሓፍ ቅዱስ “በውኑ ቆንጆ ጌጥዋን ወይስ ሙሽራ ዝርግፍ ጌጥዋን ትረሳለችን? ሕዝቤ ግን የማይቈጠር ወራት ረስቶኛል።” ይላል ኤር 2፥32። በእውኑ ሙሽራችንን ክርስቶስን ረስተነው ፣ ወደ ሚዜዎቹ አጋድለን ይሁን። እናስተውል ቆነጆ ጌጧን ፣ ሙሽራ ዝርግፍ ጌጧን እንደማትረሳ ሁሉ እለት እለት ሙሽራችንን ተዘጋጅትን መጠበቅ አለብን ። ወዳጄ የሰው ሙሽራ በሽማግሌዎች ቀጠሮ አሲዞ ነው የሚመጣው ፣ የክርስቲያኖች ሙሽራ ግን መምጫው እንደ ሌባ ነው። ስለዚህ ተዘጋጅቶ መጠበቁ እርሱ የሚሻል ነው። ሙሽራችን ክርስቶስ ይመጣል። የወስደንማል።

ሙሽሪት ሆይ መቼም አልተውሽም የለሽ ሙሽራወ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመጣል ይስደንማል።

ተባረኩ

ከታናሽ ወንችማቹ

@ymeskelu_fiker

ሚያዝያ 22 2014
1.6K viewsበርናባስ ነኝ, edited  14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 17:40:23
1.2K viewsበርናባስ ነኝ, 14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 08:44:59 ተነስቷል

        "እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ።"
የማቴዎስ ወንጌል 28 : 6

      ሰው ከወደቀበት መሬት ይነሳል፤ ሰው ህመሙ አገግሞ ከአልጋ ይነሳል፤ ሰው ከተቀመጠበት ወንበር ይነሳል። መነሳትን ለእነዚህ ዓላማዎች ብቻ ይጠቀምበታል። ሰው ከእነዚህ ነገሮች ሁሉ ተነስቶ በእግሩ ቢቆም ማንም አይገረምም አይደነቅም። ኢየሱስ ብቻ ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ።

      ሰው ተገንዞ ከተቀበረበት፤ ነፍሱ ወጥታ ስጋው በድን ከሆነበት፤ አንረሳህም በልባችን ትኖራለህ ተብሎ ድንጋይ ከተገጠመበት ውስጥ ተነሳ ሲባል ተረት ፌዝ ይመስላል። ምክንያቱም ዓለም ሁሉ በአንድነት የሚያውቀው የሞትን ኃያልነት፣ የሞትን ብቸኛ ጀግንነት፣ የሞትን አስፈሪነት ነው። ዛሬ ግን የሞት ኃያልነት ታሪክ ሊሆን ኢየሱስ በዝግ መቃብር ከሞት ተነሳ።

      ዛሬ ግን የዓለምን የዕለት ተዕለት እውቀት የሚሽር፤ የዓለምን የዘመናት የልምድ መመላለስ የሚለውጥ ክስተት ተፈጥሯል። እርሱም ሞትን ድል አድርጎ የተነሳ ሰው ተገኝቷል።

       ስንቱን አልቅሳ መሸኘት ልምዷ የሆነው ዓለም የኢየሱስን መሞት ለመቀበል አልተቸገረችም። ምክንያቱም ኢየሱስ ለእርሷ ከድሀ መንደር የተገኘ አንድ ምስኪን ሰው ነው። ይህ ምስኪን ሰው በብዙ መከራ ተደብድቦ መሞቱ አይደንቃትም። ኢየሱስ ከሞት መነሳቱ ግን ደንቋታል፣ እጇን በአፏ አስጭኗታል።

       መሬት የፈጠራትን ዋጠችው ጌታዋን ነውና አልቻለችም ተፋችው፤ ፃድቅ ነውና ሲዖል ጉልበቱ ተብረክርኮ መዝጊያው ተሰበረ። ሞት ያልያዘውን ምንም ሊይዘው አልቻለም።

       አንዲት የስንዴ ቅንጣት መሬት ላይ ስትዘራ ሞታ ትበሰብሳለች ግን በዛው አትቀርም ሺህ የስንዴ ፍሬዎችን ይዛ ትነሳለች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሞቶ ቢቀበርም ድንጋይ ቢገጠምበትም በዛው አልቀረም ሞትን ድል አድርጎ እኛንም ይዞን ተነሳ። ለክብር፣ ለህይወት፣ ለሹመት ይዞን ተነሳ።

       ከጉልበታሙ ሞት ኃይሉን ነጥቆ እኛ ደካሞቹን የትንሳኤውን ኃይል አለበሰን፤ የማስፈራቱን ሞገስ ከሞት ገፍፎ ጠላታችንን የምናስፈራበት መለኮታዊ ሞገሱን አለበሰን። ይህ ሁሉ ክብር በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ ያገኘነው ነው።

       ለህይወት ተነስተን በሞት ሰፈር አንገኝም፤ ለክብር ተነስተን እግዚአብሔርን በማያከብር ስፍራ አንገኝም፤ ለፅድቅ ተነስተን ከኃጢአት ጋር አንወዳጅም፤ ላንጠፋ ተነስተን ከሚጠፉት ጋር አናብርም፤ ለዘላለም ህይወት ተነስተን ለጊዜያዊ ህይወት አንባክንም። ክብር ለትንሳኤው ጌታ ይሁን።

  << በፈቃዱ ሞተ፣ ሞትን ይገድለው ዘንድ ሞተ፣ የሞቱትን ያድናቸው ዘንድ ሞተ፣ የተቀበሩትን ያስነሳቸው ዘንድ ተቀበረ፣ ህያዋንንም ይጠብቃቸው ዘንድ፣ ያደፉትን ያነፃቸው ዘንድ፣ ኃጥአንንም ያፀድቃቸው ዘንድ፣ የተበተኑትንም ይሰበስባቸው ዘንድ፣ የበደሉትንም ወደ ክብር ያመጣቸው ዘንድ፣ ወደ ጌትነት ይመልሳቸው ዘንድ ከሞት ተነሳ >>

      ከሞት የተነሳው ጌታ ከሞት አስነስቶናል!
1.6K viewsበርናባስ ነኝ, 05:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 04:04:35
1.2K viewsበርናባስ ነኝ, 01:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 03:49:33
1.1K viewsበርናባስ ነኝ, 00:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ