Get Mystery Box with random crypto!

የመስቀሉ ፍቅር ✞

የቴሌግራም ቻናል አርማ ymeskelu_fiker — የመስቀሉ ፍቅር ✞
የቴሌግራም ቻናል አርማ ymeskelu_fiker — የመስቀሉ ፍቅር ✞
የሰርጥ አድራሻ: @ymeskelu_fiker
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.27K
የሰርጥ መግለጫ

✞ የዚህ channel አላማ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮቶችን በማስተማር ፤ በጥልቀት የመስቀሉን ፍቅር ፤የመስቀሉን ውለታ ለአለም መናገር ፤ ለወጣቶች የሚሆን የመስቀሉን ፍቅር የሚያስረዳ ተምርታዊ ጽሁፎችን ማቅረብ እና ወጣቱን ወደ መስቀሉ ፍቅረ ማምጣት ነው፣ አላማችን።
ለሀሰብ ጥያቄ @Metsenanat

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

3

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-05-28 07:11:09 በአንተ ሙሉ ነኝ


   ወዳጆቼ አንዳንዴ ወደላይ በሃብት፣ በዝና፣ በስልጣን፣ በእውቀት የሚበልጡንን እያተመለከትን እንጎመጅ ይሆናል። አሁን የኔ ኑሮ' ኑሮ ይባላል? ምናለ እንደነርሱ ኖሬ በሞትኩ እያልን ባላዋቂነታችን ሕይወታችንን እንረግማለን።

   ወዳጆቼ ድህነት ቆሻሻ ነው የማትፈልጉትን እንድትወስኑ፤ የማትወዱትን እንድታደርጉ ያደርጋችኋል። ነገር ግን በድህነት ውስጥ ጤና ካላችሁ በድህነት ውስጥ ሰላም ካላችሁ ተመስገን በሉ።

    እንደ ባለጠጎቹ ለመሆን የተመኛችሁት ጤና ስላላችሁ ነው። የአንድ ቀን ጤና ብታጡ ከፈውስ በቀር የምትመኙት ገንዘብና ሀብት የለም።

    ወዳጄ ወደምትማልሉባቸው ሰዎች ቤት ገብታችሁ ብታዩ ባለጠግነት ሊሞላላቸው ያልቻለው ትልቅ ጉድለት፣ የሚያስነባቸው ችግር አለ። ሀብት አላቸው መብላት ግን አልቻሉም። በሽታውም አብሮ መጥቶ ይሄንን አትብሉ፣ ይሄንን አትቅመሱ ተብለው ጾም በሐኪም ታዞላቸዋል። የሐብታቸው መጠን በዝቶ እንቅልፍ ነስቷቸዋል። ሃብታቸው ሌባ ጠርቶባቸው ሰላም እንቅልፍ አጥተዋል። ኑሯቸው የመባነን ሆኗል።

   አንተን ደግሞ ሲያዩ የሚቀኑበት በርካታ ነገር አላቸው። ወዳጄ ያለህ ነገር በቂ መስሎ ካልታየህ ድፍን አለምን ብትጨብጥ እንኳ ሀዘንተኛ እንጂ ደስተኛ አይደለህም። አዳም ያለውን ሳይሆን የተከለከለው ላይ ትኩረት አድርጎ ነው ጣጣ ውስጥ የገባው። ሁሉ እያለው ማመስገን ሲገባው በተከለከለው ማጉረምረሙ ያለውን ደስታ ነጠቀው።

እናም ወዳጄቼ ያላችሁን ተመስገን በሉ። ባላችሁ ነገር ደስ ይበላችሁ። አንዱን ክርስቶስን አጥታችሁ ሁሉ ቢኖራችሁ ጎደሎ ናችሁ። ሁሉ ቀርቶ ክርስቶስ ቢኖራችሁ እናንተ ሙሉ ናችሁ። እርሱ ብቻውን በቂ ነው።

    ተመስገን ስለሰጠኸኝ ተመስገን ስለነሳኸኝም መንሳትህም በረከት ነውና። ተመስገን ከነሳኸኝ የሚጠቅም ከሰጠኸኝ የሚጎዳ አንዳች የለም። እግዚአብሄርን ሆይ በነገር ሁሉ አንተ ቡሩክ ነህ!!

ምስጋና ለስላሴ !
1.8K viewsበርናባስ ነኝ, 04:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 07:07:33 @ymeskelu_fiker
1.0K viewsበርናባስ ነኝ, 04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 06:38:04
1.4K viewsበርናባስ ነኝ, 03:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 13:04:50 "የዝማሬ ሰዓት"

ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

@ymeskelu_fiker
1.5K viewsበርናባስ ነኝ, 10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 13:02:26 የዝማሬ ሰዓት

የሚጠብቀኝ አይተኛም
ዘማሪ ይልማ ሃይሉ

@ymeskelu_fiker
1.4K viewsበርናባስ ነኝ, 10:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 13:02:13 የዝማሬ ሰዓት

በንጹህ ደሙ

ይቀላቀሉን ለወዳጆም ያጋሩት

@ymeskelu_fiker
@ymeskelu_fiker
@ymeskelu_fiker
1.3K viewsበርናባስ ነኝ, 10:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 07:14:42 እቅፍህ ዋስትናችን ነው


“እግዚአብሔር ፍርድሽን አስወግዶአል፥ ጠላትሽንም ጥሎአል፤ የእስራኤል ንጉሥ እግዚአብሔር በመካከልሽ አለ፥ ከእንግዲህም ወዲህ ክፉ ነገርን አታዪም።” — ሶፎንያስ 3፥15


     ቃላት የማይገልፃቸውን የደስታ፣ የፍቅር ስሜቶቻችንን ከምንገልፅበት መንገድ አንዱ ማቀፍ ነው። ለአንድ ህፃን ልጅ የእናቱ እቅፍ የደህንነቱ ከተማው፣ የለቅሶ መሻሪያው፣ የሰላሙ መናኻሪያው ነው። እቅፏ ውስጥ እረፍት ይሰማዋል ሁሉን እረስቶ ይተኛል።

     ለአንድ ሰው መታቀፍ ልብን ከልብ ጋር ነፍስን ከነፍስ ጋር የማነካካት ያህል ደስታን ይሰጣል። ጌታችን ሲያቅፈን እርግማንና ቅጣትን አይመጣብንም ዲያብሎስ በእኛና በቤተሰባችን ላይ ስልጣን አይኖረውም ምክንያቱም ዋስትና በሆኑ የጌታ ክንዶች ውስጥ ታቅፈናል።

      አባካኙ ልጅ ሲመለስ አባትዬው እስካሁን የት ነበርክ ብሎ ልምጭ ይዞ አልጠበቀውም። ይልቁንም እጆቹን ዘርግቶ አቀፈው። ያ የለመደው እቅፉ ዛሬም ይሞቃል ዛሬም ያ የለመደው ደረቱ ይመቻል። በዓለም ተንገላትተን ቆሳስለን ወደ እግዚአብሔር ስንመለስ ይበልህ ማን ጎርምሰህ ውጣ አለህ ብሎ ጀርባ አይሰጠንም። እጆቹን ዘርግቶ ይቀበለናል። እቅፉ ያጽናናናል፣ የደረሰብንን የነበርንበትን ደስ የማይል ሁኔታና መከራ ለመርሳት ጸጋን ይሰጠናል። በዛው መጠን የጎዱንን ያሠቃዩንን ሰዎች ይቅር የማለት ሙሉ አቅም ይሰጠናል።

      ጌታችን ኢየሱስ ትላንት ስለኔና ስለናንተ በደልና ኃጢአት እርጥብ መስቀል፣ ጥርብ እንጨት ታቅፏል፣ ብዙ ቁስሎች ብዙ ሕመሞችን መከራዎችን ታቅፏል። ዛሬ ግን እኛን ከነአቧራችን ታቅፎናል ከነስህተታችን በፈገግታ ተቀብሎናል። ትኩስ በሆነ ፍቅሩ እግሮቹ ላይ አስቀምጦናል። ይህ ፍቅር የኃጢአት አቧራችንን ያራግፍልናል የበደል ሰንኮፍን ይነቅልልናል። የጌታ ፍቅር ሰዎች ሲረግሙን እንድንወድና እንድንባርክ ያደርገናል። 

    እዚህ የፍቅር እቅፍ ውስጥ ስንገባ ይህ ፍቅር ማንም ሰው እኛን ለመወንጀል ልብ አይኖረውም።  በጣም ጥበበኛ የክርስቶስ አምባሳደር ያደርገናል።


     አቤቱ ክፉን ጋርዶ ያሻገረን እቅፍህ ነውና እናመሰግንሃለን። ስብራታችንን የጠገነልን፣ ፀፀታችንን የሻረልን፣ ስህተታችንን ያረመልን፣ መጠውለጋችንን ያለመለመልን፣ ኪሳራችንን የካሰልን ምቹው ጉያህ ነውና ተመስገን። መልካምነትህን ገፍተን፣ ቸርነትህን ንቀን፣ ፍቅርህ ኮሰኮሰን ብለን ከእቅፍህ እንዳንወጣ በግድም ያዘን። አብዝተን እንድንወድህ አይናችንን አብራልን። አሜን!!

@ymeskelu_fiker
1.8K viewsበርናባስ ነኝ, 04:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 07:13:12
1.1K viewsበርናባስ ነኝ, 04:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 22:46:03 አንባቢ ሆይ "ጸጋ" ምንድ ነው?

"ጸጋ" እግዚአብሔር ለሰዎች የሳየው ፍቅር እና ምህረት ነው። "ጸጋ" መለት እንዲው የሆነ "ነጻ ስጦታ" ማለት ሲሆነ ፤ ይህም ከእግዚአብሔር ለሰዎች የተሰጠ ነጻ ስጦታ ነው። እግዚአብሔር ጸገን ለሰዎች በነጻ(እንዲው) ሰጠ። ሰዎች ኀጢአተኛ ሰለሆኑ የእግዚአብሔርን ፍቅር እና ምህረት ለመቀበል አይችሉም። ነገር ገን ምንም እንኳን ሰው የእግዚአብሔርን ፍቅር ለማግኘት የማይገባው ቢሆንም ከእግዚአብሔር ፍቅር እና የርህራሄ ልብ የተነሳ ፣ ይህ የእግዚአብሔር ጸጋ ለሰዎች የተገባ ሆኗል። እኛ ኀጢአተኞች እና የእግዚአብሔር ጥላቶች ሆነን ሳለን እግዚአብሔር የገዛ ልጁን እንዲያድነን ወደ እኛ ላከው ፣ በገዛ ልጁም ከሞታ እና ከኃጢአት ባረነት አዳነን። (ሮሜ 5፥8) (ዮሐ 3፥16)።

ከዚህም የእግዚአብሔር ጸጋ የተነሳ ደህንነታችንን አጊንተናል። (ኤፌ 2፥8 ፤ ቲቶ 2፥11)። ደህንነት የሚገኘው በጸጋ ነው። መጽሐፍም እንደሚል “ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።” — ኤፌ 2፥9 ፤ ለማይገባው የሰው ልጅ እንዲገባ ከተገለጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ እንጂ። ከዚህ ውድ ጸጋ የተነሳም የክርስትናን ህይወት እንኖራለን። የሰው ልጅ የገኘው መንፈሳዊም ሆነ ቁሳዊ በረከቶች ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሳ ነው። እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልጁን ላከልን ፤ ቅዱሳንም ሊየረገን በጸጋው መንፈስ ቅዱስን ላከልን። ከዚም ለሰዎች ከተ ገለጠው ከተትረፈረፍው ጸጋም የተነሳ በክርስቶስ የሚያምኑ ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም ይኖራሉ።

ተባረኩ ከታናሻቹ...!!!
1.4K viewsበርናባስ ነኝ, 19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 22:46:02
1.1K viewsበርናባስ ነኝ, 19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ