2022-08-30 21:33:46
የምወደው እና የማከብረው ገጣሚ፣ ተዋናይ፣ ብዙ ነገር እና ጥሩ ሰው Wasihun Belay ዛሬ ልደቱ ነው። በሚታወቁና በማይታወቁ ብዙ ምክንያቶች የተነሳ፣ 'ገጣሚ የሚለው ማዕረግ ጥሩ ነው አይደለም' ብዬ በምወዛገብበት የጉርምስና ዕድሜዬ ከሩቅ አይቻቸው "እንደነሱም መሆን ይቻላል እኮ። እንደነሱም ተከብሮ ሙያን ማስከበር ይቻላል" ብዬ በልቤ ለምልክት አኑሬያቸው ከነበሩት ጥቂቶች አንዱ ነው። መፈጠሬን ሳያውቁ በመኖራቸው እና ደርዛቸውን በመጠበቅ ሕይወታቸው ካገዙኝ መካከል አንዱ ዋሲሁን ነው። በእኔና በግጥም መሀል ዋስ ሆኖ አሸማግሎናል። የመጀመሪያው መጽሐፌን እንዳነበበውና እንደወደደው ያወቅኩ ቀን ደግሞ፣ ፈረስ ባይኖረኝም "አበደ ፈረሴ" ብያለሁ።
ወደ ኋላ ላጠንጥንና... ከአርባት በአንዱ አርብ ቀን ፑሽኪን ከዝግጅት ታድመን ስንወጣ ከጓደኞቹ ጋር ቆመው ሲያወሩ አይቼው፣ ቆይ ዛሬ ሄጄ ላናግረው። እጅ ልንሳው። ብዬ ወደዚያ ያለ ድንጋይ ላይ ቁጭ ብዬ አፈር ላይ በእንጨት እየሳልኩ ስጠብቀው ቆይቼ፣ ቀና ብል የሉም። ሄደዋል። ያኔ ፌስቡክም የፌስቡክ ወደረኞቼም አልነበራችሁም እንጂ፣ "እርሟን ብታፈላ ጋን ሙሉ አተላ" የተባለው ለእኔ ነው ብዬ እለጥፍ ነበር። :)
መልካም ልደት ዋስዬ። እንደተወደድኽ፣ እንደተከበርኽ ኑር። ሀሳብህ ሁሉ ይሙላልህ።
@ ዮሐንስ ሞላ
97 viewsሄኖክ ተስፋሚካኤል, 18:33