Get Mystery Box with random crypto!

ሁስነል ኹሉቅ

የቴሌግራም ቻናል አርማ yeresulnfkrmeglecha — ሁስነል ኹሉቅ
የቴሌግራም ቻናል አርማ yeresulnfkrmeglecha — ሁስነል ኹሉቅ
የሰርጥ አድራሻ: @yeresulnfkrmeglecha
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 467
የሰርጥ መግለጫ

የጥሩ ጸባይ ፍቅር መግለጫ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-03-24 19:51:46 # ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ !
ሸኽ ጫሊ "ብድግ አርጎ ሲያበቃ ጊዜ!" ያሉለት ዓይነት እጣ ነው
ይሄስ! አይገርምህም ወይ ያላህ መለገስ ያሉትስ ነቢን ከመካ ወስዶ
አርሽ ላይ ማንገሱ ቢገርማቸውም አልነበር? ይሄው የሐበሻን
ሙሒብም ከቀዬው እየመራረጠ እየወሰደ በዓረብ ምድር ያነግሰዋል።
እርግጥ የአርሹም መንገድ ቢሆን ለሐበሻ ሙሒብ አቋራጭ አለው!
የመካና መዲና መሬት የሐበሻን ጀሰድና ጠረን ለምዷል። ለሙሐባው
እጅ ሰጥቷል። ነጃሺን መንገድ አስጀምሯል፤ አካቢሮቹን እነ አሕመደል
ሃዲን፣ እነ ሸኽ ዳንግላን እዛው ስቦ አስቀርቷል፤ የመከራ ጊዜ ማለፊያ
መጠለያ ናቸው ብሎ አሉኝ የሚላቸውን እንቁ ልጆቹን በአደራ
አስረክቧል።
ከበርካታ ዓመታት በፊት አንድ ጥቁር በካዕባ ማማ ላይ ወጥቶ
የጃሂልያ ጨለማን በአስገምጋሚ ድምጹ እንዲገፍና ተክቢራውን
እንዲያስተጋባ በነቢ ተመረጠ። ዓረብ አጀሙ ተደነቀ። የጌትዬውን
ዋሕዳንያ የነቢን ረሱልነት መሰከረ። ሐያቱን ሁላም ኮቴያቸውን
ሲከተል ኖረ። አሁንስ? አሁንም የኛ ሰው እዛው ካዕባ ላይ ዳግም
ነገሰ! በዳናቸው ላይ ስለመገኘታችን ደግሞ ጌትዬ ወሸሂደ ሻሂዱን
ሚን አህሊሂ እንዳለው ባለፈው ሙፍቲዋን "የነቢን ሱና አንቱ ላይ
አይተናል!" አስብሎ በነዛው ሰዎች አስመከሰከረላቸው።
አንዴ ኡስታዝ አቡበክር ዓብደላህ ነቢያችን ከነጃሺ ጋር የነበራቸውን
የመልእክት ግንኙነት በዳሰሱበት ንግግራቸው ነብያችን ለተለያዩ
ንጉሶች ደብዳቤ ይፅፉ የነበረ ቢሆንም መሊክ ወይም ንጉስ የሚለውን
ቃል የተጠቀሙት ለኛው ለሐበሻው ነጃሺ ብቻ ነበር ያሉት ነገር ጉድ
አስብሎኛል። ነጃሺም በበኩላቸው የመልስ ደብዳቤ ሲፅፉ በመተናነስ
ስሜት የረሱልን ስም ከላይ በመጀመሪያ በማስቀደም የራሳቸውን
ስም ከታች አድርገው ነበር። ሙፍቲ አንድ ጊዜ ምኞታቸውን ሲጠየቁ
የዘወትር መሻታቸው መዲናን ደጋግሞ መዘየር እንደሆነ ተናገሩ። ይሄ
ታድያ አንድ ነገር አስታወሰኝ። ኡሙ ሐቢባ ለአብረኸት ውለታ ክፍያዋን
ስትጠይቃት አብረኸት ምንም እንደማትፈልግና ለነቢ ሰላምታ ብቻ
እንድታቀርብላት ነበር የጠየቀችው። አዎን ይህ ነገር ከሙሐባና ከዲን
የሚያስቀድሙት ምንም ዓይነት ዱንያዊ ጥቅም የሌላቸውን
ሸይኾቻችንን ያስታውሳል። በሸርቅም በጘርብም "አገርኩን ካላየሁ
ሶብር የለኝም እኔ!" እያሉ በፍቅር ሲዋትቱ የኖሩትን ደጋጎች ያስተዛል።
ነቢም በወቅቱ የአብረኸትን ሰላምታ ካሉበት ሆነው መልሰዋል። ያ
መልሳቸው ለመላው ሐበሻ ደርሶ ነው ለአገሬ መሻኢኾች የሐይባ ካባ
ያስደረበላቸው የካዕባን ሐይባ ደራቢም ያደረጋቸው!
አንዳንድ ጊዜ ሳስበው ነቢ ለሐበሻ ቀድሞውኑ የመሰከሩት እርሳቸውን
በዚህ ደረጃ የሚወዱ ሙሒቦች የሚኸለቁባት ምድር መሆኗን
ጌታቸው አሳውቋቸው ይመስለኛል። ወይም ሙሒቦቹ ራሱ በዚህች
ምድር የተኸለቁት ቀድሞውንም የነቢ ዓይን ስላረፈብን ይሆናል።
የቢላልም የበረካም ባብ የኛው መግቢያ ነው። በዛም አለ በዚህ
በእርግጠኛነት የማውቀው አንድ ነገር ቢኖር ግን እንደኛ መሻኢኾች
በመደድ ባሕር ጠልቆ የሚዋኝ ቀዛፊ እንደሌለ ነው። አፋቸውን
የፈቱት፣ ጠብተው ያደጉት፣ ሐያት መውታቸውም የነቢ ሑብ ነው።
"ኢቅረዕ ኪታበከ" ሲባሉ የሚያነቡትም ይሄንኑ ጉድ የሚያስብል የነቢ
መወድስ ነው ቢኢዝኒልላሂል ከሪም!
ሐይያ ዓለሶለዋት!
ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ!
አሏሁመሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመድ
ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ ወሰለም!



                             
                                
                                      
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ   
      ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ              ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ


  
      
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡
እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ
                  
                 
              
:¨·.·¨: ❀   ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ

@yeresulnfkrmeglecha

@yeresulnfkrmeglecha

┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄
477 viewsZ, 16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-17 19:41:19 # ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ !
"ምን ይሁን ትላለህ ከዚህ የበለጠ!?" ያሉት’ኮ እንዲህ ያለ ሰርግና ምላሽ አንድ ላይ
ሲገጥምላቸው ነው። ወዲህ ለይለቱል ጁምዓ ወዲህ ኒስፉ ሸዕባን! "እንኳን እናቴ ሞታ
እንዲሁም አልቅስ አልቅስ ይለኛል!" አሉ። እንኳን የሐጃ መሙያዋን፣ የመፍፈረጃዋን
ለይለቱል በራእን አግኝተን ቀርቶ ሸዕባን በሙሉ የሶለዋት ወር ነው።
ከማ ቃለ ሷሊህ ታጁ ሠይዳችን ዓለይሂ ሶላቱ ወሰላም "ሸዕባን የእኔ ወር ነው።" ብለዋል።
የኛ ነቢ መካ ላይ ዱዓቸው ሙስተጃብ ሁኖ ጨረቃ ከሁለት የተሠነጠቀችላቸው ሸዕባን ላይ
ነው። መዲና ላይ ቂብላ እንዲቀዬር ፈልገው ቂብላው እርሳቸው እንደሚፈልጉት የሆነው
ሸዕባን ላይ ነው። መዲና ላይ ለዑመታቸው ሸፋዐ እንደሚሆኑ ብስራቱ የመጣው በዚሁ ወር
ነው። ከምንም በላይ "አሏህና መላኢካዎቹ በነብዬ ላይ ሶለዋት ያወርዳሉና እናንተም
አውርዱ!" የሚል መልዕክት ያለው የቁርዐን አንቀፅ የወረደውም እንደዚሁ። ኒስፉማ
ዒዳቸው ነው። በሸዕባን ከሁሉም ሥራ በላይ የሚወደደው ሶለዋት ማብዛት ነው። ታድያ
ሙሒብ ወራቱ "ምን ቢሞኙ ኸሚስን አይተኙ!" የተባለበት ወቅት ጋር ሲገጥምለት ሶለዋቱን
ማጋጋም እንጂ ሌላ ምን ትካርስ ከስብስ አለው? አዎ ማደግደግ ይበጃል መርቅኖ ለነቢ!
አወል ጀባ ቀህዋ ጀባ እያሉ፣ ተጎናብሰው እየኻደሙ አሚን አሚን ማለት ነው ኻድመው
ያገኙትን እጣ ጀባ!!
ምንም ነገር ብትሠራ "አዕማሉና በይነል-ቀቡሊ ወረዲሃ!" በተባለው ውስጥ ነው
የምታገኘው። እርግጠኛ አትሆንበትም ወይ ታተርፋለህ፣ ወይ ዋናህን ትይዛለህ፣ ኪሳራም
ላይጠፋው ይችላል። ኢልለ-ስ-ሶላተ ዐለል ሐቢቢ ሙሐመድ። የሶለዋት ምርጥ ዘር ግን
የትም እንዴትም ብትዘራው ዝናብ አይፈልግ ፀሀይ አይፈራ ይበቅላል፣ ያብባል፣ ፍሬ
ይሰጣል፣ በሶለዋት ታጅበው ያነሱት እጅ በባዶ አይመለስም!!
እንግዲህ በኒስፉ በሶስት ያሲን በላዕ ይታገድ፣ ሪዝቃችን ይስፋ፣ ዑምራችን ሳብ ዘለግ
ይበል በጀታችን ይፅደቅ፣ አዋጁም ፍራጁም ለ‘ኛ ይሁን፣ የሻ የሻውን ያግኝ የሚያምረው
መጀን!
ያ ሐናን ያመናን፣
ሰቢትና ዓለል ኢማን፣
ያሐናን ያመናን
ሰሊምና ዓለል ኢማን፣
አሚን ያረቢ ያ አላህ
ኻቲመል ኸይሪ ሰዓዳና። ያሉት ደጋጎች መጀን!
አዎ ዛሬማ እጣችን ይገለጥ እያሉ ያሲኑን ተባረኩን፣ ኢኽላሱን፣ ፈለቁን፣ ናስ እና ፋቲሐውን
በዬሱራው በዬፈኑ መግለጥ ነው። ዓይሻችን እንደ ሚስክ ያውድ እያሉ ሶላዋትና ዱዓውን
እንደ ወሎ ጭስ ማጓፈጥ ነው።
አዎን ዛሬ አንተኛም!
በተከበረችው፣ እጅግ ከፍ ያለ ደረጃ ባላት፣ ዱዓ የበለጠ ተቀባይነት ከሚያገኝባቸው
አምስት ሌሊቶች ዋናዋ በሆነችው ኒስፉ ሸዕባን ላይ ተገኝተናልና። በላዑ ሁሉ እንዲነሳ፣
የታመመው እንዲሽር እንዲላቀቅ ከዑዝሩ የጨነቀው እንዲፈረጅ፣ ያጣው እንዲያገኝ፣
የከፋው እንዲስቅ፣ የራቀው ኸይር እንዲቀርብ፣ ሙሐባና ጧዓ እንዲገራ፣ አገር አማን
በላው ተብሪድ እንዲሆን አሳላፊውን ይዘን በላይ ገንዳው ግርዶ እንንጎራደዳለን!
ሐይያ ዓለሶለዋት
# ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ !
አሏሁመሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ
ወሰለም!



                             
                                
                                      
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ   
      ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ              ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ


  
      
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡
እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ
                  
                 
              
:¨·.·¨: ❀   ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ
@yeresulnfkrmeglecha
@yeresulnfkrmeglecha
┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄
260 viewsZ, 16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-10 19:28:09 # ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ !
መውላና ጀላሉዲን ሩሚ "ነፍስ አእምሮ የማይረዳውን ለመስማት የራሷ ጆሮ ተሰጥቷታል።"
ይላሉ። አዎን አንዳንድ ከአእምሮ በላይ የሆኑ ነገሮች አሉ፥ ነፍሶች ብቻ ተጠቃቅሰው
የሚግባቡባቸው። አንዳንድ የፍቅር ወጎች አሉ። ጥልቅ የሆኑ፣ የአንደበት ቋንቋ ችሎ
የማይገልጻቸው፣ በነፍስ ባሕር ውስጥ ታልመው እዛው የሚፍፈቱ! የተወዳጁ ነብይ
አፍቃሪዎች ነገርም እንደዚህ ነው የሚሆንብኝ። ከስሌት ይርቅብኛል፤ ማስተንተን
ከምችለው ይገዝፍብኛል፤ ከአድማስም ከጎራም ይሻገርብኛል።
እስኪ የአንድ ወዳጃቸውን ጥግ የደረሰና በታማኝነት ያሸበረቀ የጉድ ፍቅር ላሳያችሁና
እናንተው ፍረዱኝ!
አብደሏህ ኢብን ኹዛፋ አስሰሃሚ ረ.ዓ ነቢ ለመልእክት አድራሽነት የመረጡት ታማኝ
ባለሟል ነበር። አንዴ ወደ ፐርሽያው ንጉስ ደብዳቤ አስይዘው ላኩት። በሥፍራው
እንደደረሰም ንጉሱ ደብዳቤውን ከአብደሏህ እንዲቀበል ከታዛዥ አሽከሮቹ አንዱን ላከበት።
ይህ ታድያ ለአብደሏህ የማይሆን ነገር ነበር። ፈርጠም ብሎ "አይሆንም" አለ። ምክንያቱም
ነቢ ያዘዙት ደብዳቤውን በቀጥታ ለንጉሱ እንዲሰጥ ስለነበረ በመሃል አገናኝ መግባቱን
አልወደደውም። የረሱሉሏህን ቃል ማጉደል ነው አለ። የነቢ ትእዛዝ ከሚሸራረፍ ምንም
ቢቀር የሚመርጥ ሠው ነበር። ንጉሱ ይሄ በራሱ አበሳጭቶታል። ደብዳቤው በአላህ ስም፣
ከአላህ መልእክተኛ ተብሎ መነበብ ሲጀምር ደግሞ የሚይዝ የሚጨብጠውን አጣና
ቀዳደደው። የኔ ነቢ ንጉሱ የላኩትን ደብዳቤ በእብሪት መቅደዱን ሲሰሙ ለወዳጃቸው
አንሾካሾኩ። ዘውዱ ይነቀል! በአዘል የተፈረደበት ውልግድ ነውና ጭራሽ ነቢን ይዘው
እንዲያመጡለትም ወታደሮች ልኮ ነበር። የተላኩት ወታደሮች መዲና ሲደርሱ የኔ ወልይ፣
ትልቁ ሠው ጌታቸው ያሳወቃቸውን እንዲህ አሳወቋቸው። እብሪተኛው ሠው በራሱ ልጅ
መገደሉን አረዷቸው። የማይንነካ ነክቶ ተላሰ። ኪስራ ከሰረ!መገን አብደሏህ ይህ ሁሉ
በእርሱ ሰበብ ነው’ኮ!
በነቢ ፍቅርና ታማኝነት የታነጸው አብደሏህ ነገር ቀጥሏል። በአስራ ዘጠነኛው ዓ.ሒ
ኸሊፋው ዑመር ኢብኑል ኸጧብ ረ.ዓ አብደሏህን ከባልደረቦቹ ጋር ወደ ሮማ ይልኩታል።
እዛ ደግሞ ሄርኩለስ አብደሏህን እምነቱን እንዲቀይር በውድም በግድም በበዛ ስቃይም
ሞከረው። ዓይኑ እያዬ ከባልደረቦቹ አንዱን የፈላ ውሃ ውስጥ ከተተው። ብቻውን ባለበት
ውበቷ ፈታኝ የተባለ ሴት ላከበት። እስኪደክማት ሞከረች። የጌታውና የነቢ ፍቅር ከለላ
ሆነው። ወታደሮቹ እሱን ዒላማ አድርገው ዙሪያውን ቀስት እዬወረወሩ እንዲያስፈራሩት
አደረገ። አንዱም ማስፈራሪያ ሊሰራለት አልቻለም። ሄርኩለስ ሌላኛውን ባልደረባውን
አጠገቡ ሲገሽረው ሲያይ ግን አብደሏህ ማልቀስ ጀመረ። ንጉሱ ደስ አለው። ያሸነፈ
መሰለው። አብደሏህ ግና የእንባ ዘለላዎቹ ከፍርሃት የመነጩ እንዳልሆኑ አሳወቀ።
ያስለቀሰው ነቢ ላመጡት መልእክት ቢሞት እንኳን የሚሞተው አንዴ ብቻ መሆኑ ነበር።
እናም እንድ ሽህ ነፍስ ኖሮት እያንዳንዷን ነፍሱን በነቢ መንገድ ቢሰዋ ደስታው መሆኑን
ገለፀ። ሄርኩለስ በፅናቱ፣ በጀግንነቱ፣ ላመነበት ሟች በመሆኑ እጅጉን ተደምሟል። እናም
ለውዱ አብደሏህ አንድ የመጨረሻ ምርጫ አቀረበለት። "ግንባሬን ሳመኝና በነፃ
ልልቀቅህ!" አለው። "አንድ ሠው ለራሱ የወደደውን ለወንድሙ እስካልወደደ ድረስ
አላመነም!" ያሉት ነብይ ወዳጅ የሆነው አብደሏህ ታድያ ሁሉንም ባልደረቦቹን ካልለቀቀ
ምኞቱ እንደማይሰምር አስረግጦ ነገረው። በመጨረሻም ሄርኩለስ እጅ ሰጠ። አብደሏህም
ቃሉን ፈፀመ።
አብደሏህና ባልደረቦቹ ነፃ ሆነው ወደ መነሻቸው ሲመለሱ የአብደሏህ ገድል በምድሪቷ
ቀድሞ ናኝቷል። ያኔ ኸሊፋ ዑመር እያንዳንዱ ሙስሊም የአብደሏህን ግንባር እንዲስም
አዘዙና ከራሳቸው ጀመሩ። በነቢ ኑር ያበራውን፣ ለጌታው እንጂ ለማንም ዝቅ ያላለውን
ግንባሩን ሳሙት። እንዴት ያለ ነብይ…እንዴት ያሉ ወዳጆች!!
ሐይያ ዓለሶለዋት!
# ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ !
አሏሁመሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ
ወሰለም!



                             
                                
                                      
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ   
      ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ              ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ


  
      
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡
እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ
                  
                 
              
:¨·.·¨: ❀   ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ
@yeresulnfkrmeglecha

@yeresulnfkrmeglecha

┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄
664 viewsSulle man ثايهن, 16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-03 20:28:40 # ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ !
የሸዕባንና የጁምዓ ለይል ገጠሙልን ሳብ እንሳብ ወንድም!
ሙሐመድ ኑሩ ሠላሜ ኑር ሠላሜ!
ስማቸውን ከስሙ ስላጣመረው "አላ ቢዚክሪልሏሂ ተጥመኢንኑል ቁሉብ!" ያለው
ለስማቸውም ተርፎ ነው መሰለኝ ሙሐመድ ሲባል ገና ልብን ጨምድዶ የያዘው ጘፍላ ሁላ
ይተንናል። ሶለሏህ ብለው የቀጠሉ እንደሆነ እግር ከወርች ጠፍንጎ አላላውስ ያለው
የጭንቅ ኮተት ሁላ እስምጥ ይግባ እስርጥ ሳይታወቅ ብንን ይላል። ጉዴን የማዋዬው
አለኝታዬ ነቢ!
ጀምበሬ!
እኔ ያለ ጀምበሬ የሚጨልምብኝ፣ ጎዳናው ተራራ፣ ሜዳው ገደል የሚሆንብኝ ነኝ።
ሰይዲ አደራሁን ጣሉብኝ ጥላሁን፣
ቢሆን መሃያሁን አለዛ ጦይፍሁን፣
ውዴታ የሚባል አጣብቀሁን እዳሁን፣
ደህና ነኝ መስሎኋል ታምሜያለሁ አሁን። ይላል ከላይ ደህና መስሎ ውስጡ የታመመው፣
በናፍቆት የተንገበገበውና መሻርን ፈልጎ የሚያዋያቸው ወዳጅ። የዓለሙ ዘውድ ጥላ ከሃሳብ
መከራ ሃሩር፣ ከመጨረሻውም ቀን ግለት እንደሚያስጠልል የገባው ዓሪፍ የዓሪፍ ልጅ!
በሙሐባቸው እንቅልፍ ያጣው ወዳጅ ቀጠል አድርጎም
አሳዩኝ ፊትሁን፣
እንቅልፉን ይፍጅ ዓይኔ። ይላል፥ ከጀምበር የሚያበራው ፊታቸው ታይቶ የሚሰነብት ድካም፣
የሚዘገይ ሐጃ እንደሌለ ሲያውቅ!
በኒ አደም አንድ ሕመም ሲነሳ መድኃኒት ባይኖር ኖሮ ምን ይፈጠር እንደነበረ ያስባል። እኔስ
የሚገርመኝ ሙሐመድ የተባለ መፅናኛ ስም፣ ሶለዋት የሚሉት የስሙ ማወደሻ ባይኸለቅልን
ያንን ሁሉ ስውር የውስጥ ህመም ጢሻ፣ ያንን ሁሉ የጭንቅ ዳገት፣ ያንን የደነደነ የውስጥ
የላይ የጨለማ ሸለቆ እንዴት እንሻገረው እንደነበረ ነው!
የረውዷው…!
ልምላሜው የሚያሳሳ ቅጠል ለረጅም ጊዜ ድንጋይ ተጭኖት ብርሃን ሳያገኝ ቀርቶ ልክ
ድንጋዩ ተነስቶ ሲታይ ጠውልጎና ቀለሙም ተቀይሮ እንደሚገኘው እኔም ያላንቱ ፍቅር
እንደዛው ነኝ! "ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ!" እንዲል መጽሀፉ አንቱን ካላገኘሁ ምንም ነኝ!
ሹመት ማለት ሐቢቢን ያገኙ ‘ለት፣
ዋናው ጀነት መኖር ነው ካጠገቡ። ሹመን ጌትዬ!
ያ ጀማል! ያ ጀማሉል ዓለም ፊትዎ እንኳን የኔን የቀድረ ቀላሏን የዓለምን ድቅድቅ ጨለማ
ያበራል!
ያሐቢበላህ! ቢከፋኝም ቢጨንቀኝ፣ ቢያመኝም ቢቸግረኝ የእርሶ ስም የመርዝ ሁሉ
ማክሸፊያ ሂርዝ ነው!
ነቢ የማልዶዬ ነቢ የማታዬ፣
አንቱን ባነሳሳ ሄደ በሽታዬ። ያሉት ማዲሑ መች እንዲሁ ነው?
አንቱ የጀሊል ባለሟል..!ዛሬም ሆነ ነገ የውስጤ ዝገት የሚገፈፈው ባንቱ ብርሃን ነው።
ሲራጥን በብርሃን ፍጥነት የማልፈውም ብርሃንዎን ስከተል ነው!አንዱ ማዲህ
መቼም ለቀብሬማ አንቱ ነሁ ጀዋቤ፣
አንቱን ካላገኘ አይጸዳውም ቀልቤ። ያሉትም የፊትዎም ሆነ የመንገድዎ ብርሃን ከዚህች
ምድር አልፎ ለቀብር ጨለማም የሚበቃ በመሆኑ ነው። ሌላውም "አንቱን ካላገኘሁ ሶብር
የለኝም እኔ!" ያሉት ለዚሁ ነው። እንኳን ተለይተውት አብረው እያሉም የሚናፍቀውን
ከጨረቃ የሚያበራውን ፊትዎን እያሰቡ!
ወረቴዋ ነቢ የኔማ ክብረቴ ፊትዎን ማዬቴ!
ሐይያ ዓለስሶለዋት!
# ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ !
አሏሑመሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመድ ወአላ ዓሊሂ ወሶህቢሂ
ወሰለም!



                             
                                
                                      
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ   
      ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ              ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ


  
      
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡
እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ
                  
                 
              
:¨·.·¨: ❀   ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ

@yeresulnfkrmeglecha

@yeresulnfkrmeglecha

┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄
3.0K viewsZ, 17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-27 21:50:53 አሰላሙዓለይክ ያሷሂበል ኢስራዕ ወል ሚዕራጅ!
የአርሽን ከተማ ጂብሪል የፈራውን፣
በጫማው ሄደበት ሙሐመድ ብቻውን።
የኔ ነቢ ጌትዬው በሩሑል አሚን በሰደደላቸው የጥሪ ካርድ የአርሹ ድግስ ላይ ሲሐድሩ
ምድር ሸብ ረብ ብላ ነበር። የመኽሉቃቱ ሩሕ ሁሉ በያለበት ሆኖ "ሶለሏህ ዓላ ሙሐመድ!"
እያለ አጅቧል። ፍጡር የተባለ አንድም ሳይቀር ያንን ውድ ገና በጀርባው አሳርፎ
አጃኢበኛውን ጉዞ እንዲያደርግ እጣ በወጣለት ቡራቅ ቀንቷል።
አበደን አዲስ ነው ያንቱ መወለድ እንደሚሏቸው የተሰጧቸው ተዓምራትም ሰርክ አዲስ
ናቸውና የወርሃ ረጀቡን ክስተት ሁሌም እንዘክረዋለን! ውዱ ጌታዬ ለውዱ ረሱል ሰ.ዓ.ወ
የሰጠውን ለማንም አልሰጠም!ለ‘ርሳቸው ያሳዬውንም ለማንም አልገለጠም!ከስጦታዎቹም
ሁሉ በላጩ ሲዲቁ አቡበክር ረ.ዓ ሲቀሩ ሰዎች አይደለም በእውን በህልም እንኳን
መከሰቱን ለማመን የተቸገሩበት፣ የመካ ጣኦታውያን የተሳለቁበት፣ በተከበረው ረጀብ
ከመካ እስከ አቅሷ ከዚያም ወደ ሰማዬ ሰማያት ቡራቅ ጋልበው ያደረጉትና ተኝተው
የነበረበት ፍራሽ ሞቅታው እንኳን ሳይበርድ የተመለሱበት ከስሌት በላይ የሆነው የኢስራዕና
የሚዕራጅ ጉዞ ነው።
ለዚህም ነው አባቶቻችን
አይገርምህም ወይ ያ‘ላህ መለገስ፣
መካ ተወልዶ አርሽ ላይ መንገስ። ሲሉ ግርምታቸውን የገለፁት!
መወደዱንማ ኢሳም ተወደደ፣
መወደዱንማ ኑህም ተወደደ፣
ያለ ነቢ የለም በአርሽ የሰገደ። እያሉ የነቢን ልዩ መሆን ያንጎራጎሩት!
ዓመል ሁዝን ነበር የሀዘን አመት!ነብዬ ሁለቱን ታላላቅ ድጋፎቻቸውን እናታችንን ኸዲጃን
ረ.ዓ እና አጎታቸውን አቡ ጧሊብን ያጡበት!ግና ሳይደግስ የማይጣላው ጌታዬ ሃዘናቸውን
መርሻ፣ ላጡት መካሻ፣ ውድቀት እንዳይሰማቸው የበለጠ ከፍ ማድረጊያ ሰጣቸው!
ቀልባቸው በኢማንና በሂክማ ተዘፍዝፎ በጂብሪል አጃቢነት ከቀያቸው ወደ አቅሷ ገሰገሱ።
በመስጅደል አቅሷ ነብያቱን ሁሉ አሰልፈው በኢማምነት ካሰገዱ በኋላም ወደ ላይ ጉዞ
ጀመሩ። በዬ ሰማዬ ሰማያቱ ደጆች ያሉት ጠባቂዎች በደስታ እያሳለፏቸው የነብያቱን ሁሉ
ማረፊያ እያዩ እየዘዬሩ ቀጠሉ በይቱል መእሙርን ደገፍ ብለው የተቀመጡትን አባታችንን
ኢብራሂምን ዓ.ሰ እስኪያገኙ ድረስ። አሁንም ወደ ላይ አቀኑና ጂብሪል ዓ.ሰ "አንተ ተቀደም
ከዚህ በላይ አልተፈቀደልኝም!" ያለበት ሲድረቱል ሙንተሃም ዘለቁ። ከዛም "ቃበ ቀውሰይኒ
አው አድና" በተባለው አኳኋን እስከቆሙበት ደረሱ!
ኢስራዕ ጌትዬ እንዳለው ተዓምር ነው። የኔ ነቢ ጉዞውን እንዳጠናቀቁ ስለ ተዓምሩ የሰማው
አቡ ጀህል ሰዎችን ሰብስቦ አሳቀባቸው። ሌሎቹም አምኖ መቀበል ከበዳቸው። ኡሙሃኒያ
ከነገሩ አስደናቂነት የተነሳ ስለዚህ ጉዳይ ቢያወሩ ሰዎች ዋሾ ይሏቸዋል ብላ ፈርታ
እንዳይናገሩ ሐቢቢን አስጠንቅቃቸው ነበር። ይህንን ሳይ
ወገበ ቀጭን ትከሻው ሰፊ፣
ምነው በሆንኩኝ የ'ሱ አሳላፊ። እንዳሉት ምነው እኔም ኖሬ ሰዎች ዋሾ ሲሏቸው እንደ
ሲዲቅ ባመንኩ፣ ምነው ከጎናቸው ሆኜ የአንጀተ ቀጭኗን ሴት ጭንቀት በተጨነቅኩ፣
ምነው በታላቁ ሹመት የተደሰቱትን ደስታስ ባዬሁ ብዬ እመኛለሁ!
ቢሲሪል አስራር ኢስራዕ ወል ሚዕራጅ ለሀዘናቸው መፅናኛ የላከው ጌታ ከሃም ጘም
መውጫ ይላክልን፤ ሐጃችን ይሙላ፤ ነቢ የኔ ናቸው ይበሉን!
አሏሁመሶሊ ወሰሊም ዓላ ሰይዲና ወ መውላና ሙሐመድ ወዓላ አሊሰይዲና ሙሐመድ!


                             
                                
                                      
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ   
      ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ              ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ


  
      
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡
እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ
                  
                 
              
:¨·.·¨: ❀   ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ

@yeresulnfkrmeglecha

@yeresulnfkrmeglecha

┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄
171 viewsZ, 18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-24 19:49:00 # ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ !
የኔ ነብይ የኛ ነብይ..! ሸፊዑል ሙዝኒቢን አሕመድ ኑሩ ዘይኔ!
ጌትዬ እንኳን ለታላቁ ሙሐመድ ለሌላውም ደግ ባሪያ ሲል ሁሉን ያደርጋል። ሱልጣን ኢብን
አድሃም በአንድ ማለዳ በመንገዳቸው ላይ አንድ ጥንብዝ ብሎ ሰክሮ ትውከት ያስቸገረው
ወጣት ያያሉ። የሚገርመው ግን ወጣቱ ምንም እንኳን በዛ ሁኔታ ውስጥ ቢሆንም ደጋግሞ
"አሏህ አሏህ" ይል ነበር። ይሄኔ ኢብራሂም ኢብን አድሃም ለአሏህ ስም ጥራት ተጨንቀው
እንደ አሽከር ጎንበስ ብለው አፉን ያጥባሉ። ወጣቱ ከስካር እንደነቃ ሸይኹ በሠሩት ሥራ
ተማርኮ እዛው ተውበት ያደርጋል። በዚያው ቅጽበት ያ ወጣት ከደጋጎቹ ጎን መሰለፉን
ጌታቸው ይገልጥላቸዋል። ተገረሙ፤ ተደነቁ። ጌትዬውን እዬጠየቁ መንገዳቸውን ቀጠሉ።
"ይህ ሠው ከተውበቱ በኋላ አንድም ዒባዳ የለውም። ታድያ እንዴት ከቅርብ ወዳጆችህ
ተርታ ልታሰልፈው ቻልክ?" አሉት። "አንተ ለ’ኔ ብለህ ፊቱን አጠብከው፣ እኔ ደግሞ ላንተ
ብዬ ቀልቡን አጠብኩለት!" አላቸዋ።
የዓለሙን ራሕመት፣ በእዝነቱ ለእዝነት የላከውን፣ ዓይነታውን ሙሐመድ፣ ኸልቁን
አሷራፊውን፣ ወዳጁን ከርራሚውን፣ "ዑመቲ ዑመቲ" ብሎ ታጥቆ የሚያነባውን ነብይሳ?
ሰይደል ዓረቢ ወል አጀም፣ ጂስሙሁ ሙቀደስ ሙዕጦር ሙጥሀር፣ ሙነወር ፊል በይቲ ወል
ሐረም፣ ሸምሱዱሃ በድሩ ዱጃ፣ ሶድረል ዑላ፣ ኑረል ሑዳ ብለው የሚያወድሱትን ገበርሳ?
አንድ ደግ ሠው እንዲህ አሉ። "ነቢ በመናሜ ዘዬሩኝና አንድን ጥያቄ አነሳሁላቸው። ያ
ረሱለሏህ በአንድ ሶለዋት አሏህ አስር ሠላም የሚያወርድባቸው ሙእሚኖች ከልባቸው
ተመስጠው ሶለዋት የሚያወርዱትን ነው ወይስ በምላሳቸው ብቻ የሚያነበንቡትን? ረሱሉ
መለሱ። ‘ልጄ ሆይ በምላሳቸው ያለ ተፈኩር የሚያወርዱት ናቸው የአሏህን አስር ሶላት እና
ሰላም በምላሹ የሚቋደሱት። እነዚያ በኔ ላይ የተመስጦ ሶለዋትን የሚያወርዱትማ
የጀባታቸውን መቃም አሏህ እንጂ ማንም አያውቀውም’!"
ባደፈ ቀልባችን፣ ባልጠራ አንደበታችን፣ በሚንጎላጀጅ ዓይናችንም ቢሆን፣ ጥሪው ሸርጥም
ባይሞላ ስንጠራችሁ አትቅሩ እያልን አርሒቡ እንላለን አርሂቡ ነቢ ግቡልን። አይጠዬፉንም፤
ጌትዬውም ስማቸውን ሰምቶ በባዶ አይመልሰንም። መለኪያው፣ ሚዛኑ እኛ ሳንሆን
ሙሐመድ የሚለው ትልቁ ሥም ነው። "ዓለሙን ለርሱ ሲል የኸለቀው ጀሊል!" እንዳሉት
ለሙሐመድ ሲባል ሁሉ ይሆናል!
ያልነው ሁሉ ይሁንልን ነቢ መጀን!
ታግ የተደረጋችሁት በምክንያት ነው ውዶቼ! ከመሰሎቻችሁ ጋር ሁሉ የሶለዋቱ ሰዋብ
ይድረሳችሁ፤ አርሽ የተንቀጠቀጠለትን ወጣት ሶሀባ እጣ ለናንተ ያርገው፤ የዑማው አውራ፣
የዲኑ ዋልታና ማገር ያድርጋችሁ!እወዳችኋለሁ!
ሐይያ ዓለ ሶለዋት
# ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ !
አሏሑመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ ወሰለም!



                             
                                
                                      
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ   
      ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ              ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ


  
      
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡
እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ
                  
                 
              
:¨·.·¨: ❀   ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ

@yeresulnfkrmeglecha

@yeresulnfkrmeglecha

┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄
158 viewsZ, 16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-23 19:49:04 ሚዕራጅ --- የንግስናው ጉዞ --- 2
ሠይዲን ( ሠ.ዐ.ወ ) ጨምሮ መላ ፍጥረተአለሙን የፈጠረው ታላቁ ጌታ -- አሏህ ---
በዛች ቅፅበት እንዲህ የሚል መልዕክት ለጅብሪል አስተላለፈ ....
" የእኔ ወዳጅ -- ከፈጠርኩት ሁሉ ምርጡ -- ዑሙ ሃኒያ ቤት በትዕቢተኞች ዘለፋ ቀልቦ
ተሠብሮ ተኝቶል።
ጅብሪል ሆይ !!! ሂድና ወዳጀን አምጣው ። ታላቅ ግብዣ እንዳሠናዳንለት ንገረው ።
ጅብሪል ሆይ ሂድና ለሚካኤልም ንገረው --- የሠጠነውን ሁሉንም ስጦታ ለዚህ ግብዣ
እንዲጠቀምበት አስረዳው ።ለእስራፌልም ንገረው --- ለአንድ ሠዐት ያኽል ያለ ማቆረጥ
የደስታ ጥሩንባውን እንዲነፋ ።
ጅብሪል ሆይ ሂድና ለእዝራኤል ንገረው በዛሬው ለሊት አንድም ሩህ እንዳያወጣ ።ማንንም
ሠው እንዳይገድል አስጠንቅቀው ።
ጅብሪል ሆይ በዛሬው ለሊት አንድም ሠው ቀብር ላይ እንዳይቀጣ ለነኪርና ለሙንከር ሂደህ
ንገራቸው ። ጅብሪል ሆይ ለሪድዋንም ሂደህ ንገረው ጀነትን ከመቸውም ጊዜ በበለጠ
እንድታምርና እንድትዋብ ያርግ ።ጅብሪል ሆይ ለከሮብዬችም ንገራቸው ዝቅ ብለው
ተናንሠው ወዳጀን እንዲኽድሙ ።
ጅብሪል ሆይ 70 ሺ መላኢካ አስከትለህ ክንፎችህን በሙሉ ዘርግተህ ጀነት ውስጥ ግባና
ካሉት ቡራቆች ለዚህ ጉዞ የተመረጠውን እድለኛ ቡራቅ ያዝና ወደ ኡሙ ሃኒያ ቤት ሂድ ።
እዚያ ወዳጀ ተኝቶል ። ግብዣየን ንገረው ።ወደ እኔም ይዘህው ና ።ልየውና ናፍቆቴን ልወጣ
። እርሡም ይየኝና ስብራቱን ይጠግን። ወደ እኛም ይቅረብ ። ከፍተኛ የሆነ
መስተንግዶችንና አክብሮታችንን ይወቅ ....


ይቀጥላል



                             
                                
                                      
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ   
      ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ              ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ


  
      
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡
እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ
                  
                 
              
:¨·.·¨: ❀   ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ
@yeresulnfkrmeglecha
@yeresulnfkrmeglecha

┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄
153 viewsZ, 16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-22 19:18:47 ሚዕራጅ --- የንግስናው ጉዞ -- ክፍል አንድ
ረጀብ 26 ቀን ላይ ሠይዲ( ሠ.ዐ.ወ) ብቻቸውን ወደ ካዕባ አመሩ ። የተወሠነ ሠዐታት
ከጌታቸው ጋ ለማውራት አንድ ኩርባ ላይ ተቀመጡ። በተመስጦም ጌታቸውን የልባቸውን
መሻት እየነገሩት ሳለ አቡ ጃሃል ከብዙ ተከታዮቹ ጋ መጣና እንዲህ አላቸው " ሙሃመድ
ሆይ አንተ ነብይ ነህ እንዴ ? አዎ አሉት በልበ ሙሉነት ። እርሡም እና ብቻህን እዚህ ምን
ትሠራለህ ? የታሉ ተከታዮችህ ? የታሉ ረዳቶችህ ? እንዲህ በብቸኝነት ሚቆዝም ነብይ
አይተን አናውቅም ። እኔን አታየኝም እንዴ ስንት አጀባ ስንት ተከታይ ስንት ረዳት አስከትየ
እንደምጎዝ አንተ ነህ እኔ የተላቀና የተከበረ የምንመስለው .... እያለ የትዕቢት ቃላቶችን
አዘነበባቸው ...." አቡ ጃሃል ይህን ተናግሮ እንዳበቃ ሌላ የቁረይሽ ባለባት መጦ ተመሳሳይ
አይየት መልዕክት ያለው የትዕቢት ንግግር ተናገራቸው ። በዛች ቀን ሆን ብለው ሠባት
የተለያዮ የቁረይሽ ባላባቶች የሠይዲን ቅስም ለመስበር የትዕቢት ቃላቶችን እየተለዋወጡ
አጎረፉባቸው ።
ሠይዲ ( ሠ. ዐ.ወ) ከፋቸው ። ቀልባቸው ስብር አለ።እንዲህ ሲሉም ለራሳቸው አንሾካሾኩ
" ይህን ሪሳላ ከጀመርኩ 12 አመት ሆነኝ ። እነዚህ የቁረይሽ ባላባቶች እንኳን ባመጣሁት
ዲን ሊያምኑ ይቅርና "የነብይነት " አላማና ተግባር ምን እንደሆነ እንኳን ሊረገዱ አልቻሉም
። ይህ አሳዛኝ ነገር ነው ብለው ቀልባቸው ስብር አለ። "
ቀን እንደዛ ቀልባቸው ተሠብሮ እዛው ካዕባ ላይ ውለው ማታውኑ በሶፋና መርዋ መሃል ላይ
ወደ ሚገኘው ሠኞ ለሊቱ ረጀብ 27 ወደ ዑሙ ሃኒያ --- የአቡ ጧሊብ ልጅ --- የአልይ እህት
ቤት ሄዱ ። ቀልባቸው እንደተሠበረ ዑሙ ሃኒያ ገብቶታል ። ምን ሁነው ነው ብላ
ጠየቀቻቸው ። የሆነውን ሁሉ ነገሮት። እርሶም ብልህ ሴት ስለነበረች እንዲህ አለቻቸው "
ወላሂ አንቱ እውነተኛ እንደሆኑ ሁሉም ሠደቢዎቹ ያውቃሉ። ነብይ እንደሆኑ ሁሉም
ባላንጣዎቹዎ ያውቃሉ። የአንቱን ትክክለኛነት ዛሬ አይቱን ዝቅ ለማድረግ የትዕቢት
ንግግሮችን የተናገሩት በሙሉ ያውቃሉ። ነገር ግን ምቀኝነት ነው እንዲህ ሚያረጋቸው ።
ትዕቢትና ሂስድ ነው እንዲህ ያበላሻቸው ።ውስጣቸው የቆሸሸ ስለሆነ ነው እንዲህ አንቱን
ለመዝለፍ ያነሳሳቸው .... " እያለች ዑሙ ሃኒያ አፅናናቻቸው ። በዑሙ ሃኒያ ንግግር
የተወሠነ ተረጋጉና ኢሻን ሠግደው ሙሉ ለሙሉ የተሠበረው ቀልባቸው ሳያገግም እዛው
ላይ ሸለብ አሉ ....

ይቀጥላል.....



                             
                                
                                      
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ   
      ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ              ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ


  
      
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡
እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ
                  
                 
              
:¨·.·¨: ❀   ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ
@yeresulnfkrmeglecha
@yeresulnfkrmeglecha
┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄
142 viewsZ, 16:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-20 20:09:26 የዙህር ሰላት ደርሶ ቢላል አዛን እያደረገ ነው። ነቢም ሰ ዐ ወ እያደመጡ ነበር። የቢላልን አዛን እየተከተለ እዛን የሚል ሰው ድምፅ ከርቀት ይሰማል።

ቢላል አዛኑን ካጠናቀቀ በኋላ ረሱል ሰዐወ፦‹‹ማን ነው አዛን ሚለው ከወደ ውጭ በኩል? ›› ሲሉ ጠየቁ። አባ መሕዙራ የተባለ እረኛ በማላገጥ ስሜት አዛን እያለ ግመሎቹን እንደሚያግድ ነገሯቸው።

ረሱልም ሰዐወ በተረጋጋ ስሜት ይህ ሰው ተይዞ እሳቸው ዘንድ እንዲቀርብ ዐሊይን እና ዙበይርን ላኳቸው። ሁለቱም ወደተላኩበት ሂደው አላጋጩን ከነ ግብረ-አበሮቹ ጠፍረው አመጧቸው።

ሁሉም አቀርቅረው ረሱል ሰዐወ ፊት ቆሙ።
‹‹ ከናንተ ውስጥ ማን ነበር አዛን ሲል የነበረው?›› ረሱል ስዐወ ጠየቋቸው።
ፍርሀት ስላደረባቸው ሁሉም ዝም አሉ።

ዝምታቸውን ያስተዋሉት ነቢይም፦‹‹እንግድያ ማን አዛን እንዳለ ለመለየት እያንዳንዳችሁ በየተራ አዛን በሉ›› አሏቸው። ሁሉም አዛን ካሉ በኋላ የአባ መሕዙራ ተራ ደርሶ አዛን ሲል እሱ መሆኑ ታወቀበት።

‹‹ስምህ ማን ነው?›› አሉት ነቢ ወደሱ ጠጋ ብለው።
‹‹አባ መሕዙራ እባላለሁ›› አለ ፈራ ተባ እያለ።
‹‹የመልአክ ድምፅ ይመስል እየተጠበብክ አዛን ትል የነበርከው አንተ ነህ?›› ነቢ ጠየቁት።

ቅጣቱን ለመቀበል ሲዘጋጅ የነበረው ሙሽሪክ በቅጠቱ ፈንታ ይህንን ልብ የሚማርክ ንግግር ሲሰማ ውስጡ ተናወጠ። ረሱል ሰዐወ ከአላጋጩ እረኛ ፊት ቁመው በጭንቅላቱ የጠመጠመውን ፎጣ ከጭንቅላቱ ላይ አውልቀው ፀጉሩን እየዳበሱ፦‹‹አላህ በረካ ያድርግህ፣ ወደ እስልምናም ልብህን ይምራልህ›› አሉት።

በስብዕናቸው የተማረከው አላጋጩ እረኛም የመልዕክተኛው እጅ ከራስ ቅሉ ሳይወርድ ጓደኞቹ እየተመለከቱ ሸሀዳውን ያዘ።

የድምፁን ውበት የመሰከሩለት ይህን እረኛም ረሱል ሰዐወ ወደ መካ ሂዶ አዛን እንዲል ሾሙት።ከዝያች ቀን አንስቶ ወደ መካ የተመመው ይህ እረኛም የመካ ሙአዚን ሁኖ‹‹ነቢ የዳበሱትን ፀጉር መቼም አልላጨውም›› ሲል ስለት ተሳለ።

መካ ላይ ቁጭ ብሎም እስከ እለተ ሞቱ ድረስ የነቢን ሰዐወ ትዕዛዝ እየፈፀመ ከረመ። ከሱ ህልፈት በኋላም ልጆቹ እና የልጅ ልጆቹ ለ300 አመታት ያህል መካ ላይ አዛን ይሉም ነበር።



ምንጭ፦

سنن النسائي
سنن ابو داود
مسند أمام احمد



  
      
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡

እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ
                  
                 
              
:¨·.·¨: ❀   ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ
@yeresulnfkrmeglecha

@yeresulnfkrmeglecha

┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄
152 viewsZ, 17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-27 19:54:31 # ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ !
ውዴታው ያደርጋል ሀያራ ሱካራ፣ ዐርሽን የዘመተው እነ ጅብሪል ጋራ፣
አይተነው እንሙት ያገርኩን ተራራ!
ጌትዬው ነቢን ቢወድ ከሞቀ ፍራሻቸው ላይ በሌሊት አስነስቶ
አግኝቷቸው ነበር። እርሳቸውም በይተል መቅዲስ ለመድረስ ከመካ
ሲነሱ ጨርቄን ልሰብስብ፣ ማቄን ልሸክፍ አላሉም። የርሳቸው ፍቅርም
ወዳጆቻቸውን ሊጎርሱ የጠቀለሉትን አስጥሎ፣ የአልጋውን ሙቀት
አስትቶ፣ ኑረቱም ትድረቱም ለምኔ አስብሎ ነበር የሚያስጋልባቸው።
ከኡሑድ ዘመቻ በፊት እንዲህ ሆነ… ሠይዱና ሃንዘላ ረ.ዓ አዲስ
ሙሽራ ሆኖ የመጀመሪያውን ሌሊት ከተወዳጅ ባለቤቱ ጋር እያሳለፈ
ነው። እጅግ ትወደው ነበር። እሱም ይሳሳላታል። ለርሷ ያች ምሽት
እስከ እለተ ሞቷ ድረስ የማትረሳት የሕይወቷ አስደሳች ጊዜ ነች።
የደስታን ባሕር በፍቅር ጀልባ እየቀዘፉ፣ ተነፋፍቆ በመገናኘት ወጀብ
እየተላጉ ነበር ያመሹት። ደስ ብሏት ትስቃለች፤ ዓይኖቹ በስስት ጥርሷ
ጋር ተተክለው ይቀራሉ። ግና በቅጽበት ነገሮች ተለዋወጡ።
ምን ተፈጠረ?
ሃንዘላ ወደ ኡሑድ ዘመቻ እንዲሄዱ ለዘማቾች የሚደረገውን ጥሪ
ሰማ። ጀነትን በዱንያ ካስመለከተው የሞቀ መኝታው ላይ ተስፈንጥሮ
ለመነሳት አላመነታም አፍታም አልፈጀበትም። ነብዬ ተጠቁብኝ ብሎ
እየበረረ ከቤቱ ወጣ፤ በዚህ ምድር ላይ ካለ ነገር ሁሉ አብልጦ
ለሚወደው የነቢ ገላ ጋሻ መከታ ከለላ ልሁን ብሎ ሲከንፍ ደረሰ፤
"ዓልይም በቦታው ተኛለት ሊሞት" እንደተባለው ከገዛ ሕይወቱም
በላይ አብዝቶ ለሚሳሳለት ነብይ ቤዛ ሊሆን ተጣደፈ፤ ከመጣደፉ
ብዛት ግዴታ የሆነበት ጙስል ( ትጥበት) እንኳን ትዝ አላለውም።
ታድያ ከዘመቻው መጠናቀቅ በኋላ ሃንዞላ ከተመላሾቹ አልሆነም፤
ተሠዋ። ረሱሉሏህ ﷺ መላኢካዎች ትጥበቱን ሲያደርጉለት
ተመልክተዋል። ሶሀባዎች ከአካሉ የሚንጠባጠብ ውኃ አይተው
ተደንቀዋል። ሚስቱ ነገሩን ስትሰማ ልቧ ተሰበረ፤ ባዶነት ተሰማት፤
የራሷን ሕይወት ያጣች መሰላት። የልቧን ንዳድ ያከሰመው፣ የውስጥ
ቁስለቷን ያከመው የሆነው ሁሉ ለነቢና ይዘውት ለመጡት የብርሃን
መንገድ ሲባል በደስታ የተከፈለ መስዋዕትነት መሆኑን ማስታወሷ
ነው። ከዛስ ምን አደረገች? እርሱ በጀነትም አብራው ልትሆን
የምትከጅለው ብቸኛው ሰው ነውና ሌላ ላታገባ ወሰነች።
ተግብራውም ኖረች። በነቢና ሙሒቦቻቸው መንደር ሕይወቱም
ህልፈቱም የፍቅር ነው። "ወዳጁን ገዳይ እንዳንቱም የለ ወረቴ!" አሉ
ሸኾቹ..!
ሐይያ ዓለ ሶለዋት!
# ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ
አሏሑመሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመድ
ወዓላ አሊሂ ወሶሕቢሂ ወሰለም!




ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ





ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡

እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ



:¨·.·¨: ❀ ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ
@yeresulnfkrmeglecha

@yeresulnfkrmeglecha

┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄
721 viewsSulle man ثايهن, 16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ