Get Mystery Box with random crypto!

#ኸሚስ_ከአረፋ ለይል ጋ ገጠመልን የዳና ሀሪማ የመጀመሪያ-ዙር ተማሪዎች አንድ ዕለት ሼህ አህ | ሁስነል ኹሉቅ

#ኸሚስ_ከአረፋ ለይል ጋ ገጠመልን

የዳና ሀሪማ የመጀመሪያ-ዙር ተማሪዎች

አንድ ዕለት ሼህ አህመደ-ዳንይ ተመስጠው፣ ፊታቸውን ለፈጣሪ አስጥተው፣ ቁጭ ብለው ነበር። ከተከታዮቻቸው ጥቂቶቹ፣ ወደ እርሳቸው ገቡ።
ጥርስ ሙሉ ፊታቸውን እየመገቡ -«ሼሆቹ! አረዳው(ባላገሩ) አርባ ጊደሮችን በስጦታ አስረክቧል። "ዱዓ አድርጉልን"ም ብሏል።» አሉ።

ሼህ አህመድ ደርባባነታቸውን አከሉ። አልተከፉም፣ አልተደሰቱም - «እንዲያ አደረጉ?» ብለው የሰባ ገረሜታ አቀበሉ። ወዲያው ባለጊደሮቹ እንዲጠሩ አስደረጉ። ሰዎቹ ተሰበሰቡ።

«አርባዎቹን ጊደሮች፡ በአርባ ልጆች ቀይሩልኝ?» አሏቸው። «ላስተምራቸው። ለእርሻ፣ ከብት ለመጠበቅ፣ ወንዝ-ወርዶ ውሃ ለመቅዳት ስትፈልጉ ወደ እናንተ ይመጣሉ። ከዚያ በተረፈ ጊዜያቸው ከእኔው ያሳልፋሉ። በዚህ ተስማሙኝ?» አጥብቀው ጠየቋቸው፣ ሼህ አህመድ።ለልባዊ ምኞታቸው እውኔታ ተማፀኗቸው።

ባላገሮቹ ጊደሮቹን ወሰዱ። የተጠየቁትን በ‹መርሃባ› ፈቀዱ። ልጅ ልጆቻቸውን እያመጡ አስረከቡ።

የሼህ አህመድ፣ በዳና የመጀመሪያ-ዙር ተማሪዎቻቸው ሆኑ - እኒያ አርባ ልጆች። የተማሩት የቁርአን ነቢብ ብቻ ነበር። ከእርሳቸው ንጥር ግብርና ምግባር ግን፣ አንፀባራቂውን እስልምና ይዋሀዱት ጀመር። እንዳለ ቀዱት። ሳያስቀሩ ወሰዱት።

ሼህ አህመድ ሆን ብለው ነበር ወጥመዱን የጣሉት። አንዱን ትውልድ በጥበብ አጠመዱት። ልጆች ወደ ወላጆቻቸው ሲሄዱ ነቀፌታ ተደፋፈሩ። መረን የለቀቀ ተግባራቸውን - «ይህንንማ ሼሆቹ ወንጀል ነው ብለዋል፡ እርሱንማ ክልክል መሆኑን አስተምረዋል» እያሉ ተቃወሙ። ወላጆችም «እርሳቸው ካሉማ» በማለት፣ ወደ ሼህ አህመድ ማምራት ጀመሩ። ጥያቄ እየያዙ፣ በአጥጋቢ መልስ እየወዙ እምነታቸውን እንደገና ተማሩ። በሼህ አህመድ ጥበብ!

ዳናዎች ቅፅ ፩ ፡ ኸድር ታጁ
ገፅ 93



 


                             
                                
                                      
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ   
      ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ              ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ




  
      
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡

እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ
                  
                 
              
:¨·.·¨: ❀   ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ
@yeresulnfkrmeglecha

@yeresulnfkrmeglecha

┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄