Get Mystery Box with random crypto!

# ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ ! ሳሙና አድርጎታል ስምኩን ለወንጀል! 'ሰይዲ በሀሳብ ነውጥ ዉስጥ ሆነው አ | ሁስነል ኹሉቅ

# ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ !
ሳሙና አድርጎታል ስምኩን ለወንጀል!
"ሰይዲ በሀሳብ ነውጥ ዉስጥ ሆነው አይተናቸው ምን እንዳሳሰባቸው
ብንጠይቃቸው
‘መካ ዉስጥ ሰላምታ ያቀርብልኝ የነበረ ዛፍ ታዉሶኝ ነዉ’ አሉ፡፡" ብለው
ተናገሩ አቡ ሁረይራ። ይህን መልዕክት ያነበቡት ሸክ ኢማም ጁነይድም
"የዛፍን ሰላምታ ያስታወሰ ነብይ ያንተን ሶለዋት እንዴት ይዘነጋት?" ይላሉ
፡፡ አንድም ትሁን ችላ የማይሉት የህዝባቸዉን ሰላምታ መሆኑን ያወቀስ
እንዴት ሰላምታዉን ይነፍጋል???
አሁንም ቅድምም፣ ዛሬም ነገም አሏሁመ ሶሊ አላ ሀቢቢከ ኸይሪ
ኸልቂክ! አልፉ ሶላት ወሰላም አላ ነቢቢ…አልፉ ሶላት ወሰላም አላ
ነቢቢ ሰይዲ ያረሱለሏህ! ዝዝዘህ!

ሱፍያኑ ሰውሪይ ሲቆምም ሲሄድም ሲቀመጥም ሲነሳም የወለላዬን ስም
ካፉ የማይለይን፣ ሌላ ዚክር የሌለ እስኪመስል ድረስ በርሳቸው ላይ
ሰላምታ በማውረድ የተጠመደን አንድ ወጣት አይተው በመገረም
ሚስጥሩን ቢጠይቁት የሆነውን ጉድ ና ልንገርህማ ጓዴ!ወጣቱ
ሚስጥሩን ያጫወታቸው እሳቸው መሆናቸውን ሲያስረግጥ ነው። የፍቅር
ነገር ሁሉ አይገባውማ!!
ከአባቱ ጋር ለሃጅ ጉዞ እንደወጡ ጉልበቱ የተዳከመው አባት ያሰበበት
ሳይደርስ ታመመና ጠንቶበት ወደ አኸራ ተሻገረ። ያም ብቻ አይደለም፥
የሚያምር የነበረው ፊቱ ከመቅጽበት ጽልመት አጠላበት። በዛ ምድረ
በዳ ይህ መከራ የወደቀበት ወጣት የሚያደርገው ግራ ገብቶት አዝኖ
በተቀመጠበት ድንገተኛ እንቅልፍ ሸለብ አደረገው።

በህልሙም ግርማ ሞገስ ያለውና የሚያምር ሰው ወደ አባቱ ራስ
ተጠግቶ በኑር እጁ ድብስብስ እያደረገ የጠቆረውን ፊቱን በፊት
ከነበረውም ይበልጥ ሲያስውበው ተመለከተ። "ማነህ?" ብሎ ሲጠይቅ
ነው ሚስጥሩ የገባው።
"እኔ ሙሐመድ ነኝ
ወዳጅ የምረዳ አላህ አግዞኝ!" አሉት። የሟቹን ፊት ያጠቆረው ወንጀሉ
እንደነበረ ግና የማይካድ ሃቅ አንድ ውብ ሥራ እንዳለው እሱም ሶለዋት
እንደሆነ ነገሩት!ጠቃሚ አካውንት!! አክለውም "መጥቼም መርዳቴ
ለዚሁ ምላሽ ነው፤ ሶለዋት ላበዛ አማልደዋለሁ፤ ዋስም እሆነዋለሁ፤
ወንጀሉንም አስምራለሁ…"እያሉት ሳለ ቢባንን በህልሙ ያዬው እውን
ሆኖ የአባቱ ውበት ተመልሶ መጥቶ አገኘው። እንግዲህ ከዛን ቀን ጀምሮ
ነው ከሶለዋት ቦዝኖ የማያውቀው።

ሰይዲ ወያሰነዲ!ስምዎ በዱንያ ሹመት ማ’ረጌ ወዲያ ደግሞ ዓዛብን
መሻገሪያዬ ነው!መለከል መውት ሲመጣ፣ ስታጠብም፣ ስከፈንም
በለሕድም በሲራጥም ይረዳኛል!ሸፊዑል ሙዝኒቢን! "ምን እንኳን ባልረባ
ሥራ ባይኖረኝ!" እንዳሉት "በስሙ ተማሩ አቡና አደሙ" እንደተባለውም
ነብያት እንኳን ዋስትናዎን ፈልገው "አኳኋኔን አይተሽ እንድትነግሪልኝ!"
ብለው እናታችን አሚና ጋር መለስ ቀለስ እንዳሉት ሁሉ እኔም
ልመዝገብ፣ ባለሟል ልሁን!
# ሶሉ_ዓለል_ሃቢብ !
አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪከ ዓላ ሰይዱና ወመውላና ሙሐመድ!

https://telegram.me/yeresulnfkrmeglecha