የዲጂታል ባንክ አግልግሎት ሙሉ በሙሉ መጀመሩን ንግድ ባንክ አስታወቀ
በሲስተም ችግር ምክንያት በባንኩ አገልግሎቶች ላይ ማለትም በቅርንጫፎች፥ በኢንተርኔት ባንኪንግ፥ በሞባይል ባንኪንግ፥ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ አጋጥሞ እንደነበር መግለፃችን ይታወቃል።
በቅርንጫፍ እና በኤቲኤም የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀደም ብለው መጀመራቸውን ያሳወቅን ሲሆን አሁን ደግሞ በዲጂታል የሚሰጡ የባንክ አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ መጀመራቸውን እናሳውቃለን።
ውድ ደንበኞቻችን በትእግስት ስለጠበቃችሁን እያመሰገንን ለተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል በድጋሚ ይቅርታ እንጠይቃለን።
@Yenetube @Fikerassefa