አምቦ ከተማ ተማሪዎች ሰልፍ ወጥተዋል! አምቦ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ እና መሰናዶ | YeneTube
አምቦ ከተማ ተማሪዎች ሰልፍ ወጥተዋል! አምቦ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ እና መሰናዶ ተማሪዎች፤ ፍትህ ለሀጫሉ፣ የታሰሩ ፖለቲከኞች ይፈቱ፣ እና ሌሎች መፈከሮችን በማሰማት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸውን የአዲስ ዘይቤ መረጃ ያመለክታል። ሆኖም ሰልፉ ብዙም ሳይቆይ ተማሪዎቹ በፖሊስ ሀይሎች እንደተበተኑ እና አንዳዶችም እንደታፈሱ ከአይን እማኛችን ለማረጋገጥ ተችሏል።አዲስ ዘይቤ አምቦ ያለውን የፖሊስ ቢሮ ለማነጋገር ሙከራ ያደረገ ቢሆንም "ስብሰባ ላይ ነን አሁን ማናገር አንችልም" የሚል ምላሽ አግኝቻለው ብላለች።
@YeneTube @FikerAssefa