ስልሳ ስምንት ዜጎች ከሊባኖስ ቤይሩት ወደ አገራቸው ተመለሱ።
ዛሬ ጥር 28 ቀን 2013 ዓ.ም ስልሳ ስምንት ኢትዮጵያዊያን ከሊባኖስ ቤይሩት በፍሪደም ፈንድ እና አጋር ኢትዮጵያ በተባሉ አገር በቀል በጎ አድራጎት ድርጅቶች አማካኝነት ወደ አገራቸው ተመልሰዋል።
ወደ አገራቸው የተመለሱ ዜጎችን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቆንስላ ጉዳዮች ዳይረክቶሬት ጄኔራል ተወካይ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው ለተመላሾቹ አቀባበል ማድረጋቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa