Get Mystery Box with random crypto!

#ነብዩሏህ_ኢብራሂም_እና_እስማዒል ክፍል እንደምትደሰት በሚገባ ካስ | የነቢያት ታሪክ እና እስላማዊ ትምህርቶች

#ነብዩሏህ_ኢብራሂም_እና_እስማዒል

ክፍል

እንደምትደሰት በሚገባ ካስረዳችው በኋላ ኢብራሂም ሃጀር የተባለችውን
አገልጋያቸውን አገባ።
ከእለታት አንድ ቀን ኢብራሂም ከሳራ ጋ በሚኖሩበት ድንኳን አጠገብ ሶስት
ወጣቶች ኢብራሂም እና ሳራ ቁጭ ባሉበት መጡ'ና ሰላም አሉት።እሱም
ሰላምታቸውን መለሰላቸው'ና ወሬ ሳያበዛ አንድ ሙኩት አርዶ ጠባብሶ
አቀረበላቸው። አቦ ወላሂ ይመቸው እንግዳን በወሬ ከማድረቅ በፊት ምግብ
ሲቀርብ ነው ሙድ ያለው..
ኢብራሂም ምግቡን ካቀረበ በኋላ እጃቸውን ቢያይ ቢያይ ምንም ወደ ምግቡ
አይዘረጉም።ይህን ግዜ ኢብራሂም በልቡ ፍራቻ አደረ።
ሊዘርፉኝ የመጡ ሌቦች ናቸው!!!?
ወይስ ሊገድሉኝ..!!?
ወይስ ሚስቴን ሊተናኩሉ ነው..!!? እያለ ይጨነቅ ጀመር።
ኢብራሂምም፦"ምን ፈልጋችሁ ነው እነ ማን ናችሁ?" ብሎ ጠየቃቸው።
ወጣቶቹም፦"እኛ ከሰማይ የመጣን መላዕክቶች ስንሆን ላንተ ልጅ
እንደምትወልድ ልናበስርህ እና የሉጥን ህዝቦች ልናጠፋ ነው የመጣነው"
ሲሉት
ኢብራሂም ሚያላግጡበት መስሎት በመገረም፦"ይህ እንዴት ይሆናል? እኔ እኮ
የጃጀው ሽማሌ ነኝ" አላቸው።
እነሱም፦"ይህ የጌታህ ትዕዛዝ ነው እሱ ባሻው ነገር ላይ ቻይ ነው" ብለው
መለሱለት።
ይሁን ሁሉ ንግግራቸውን ስትሰማ የነበረችው ሳራ ከት ብላ ሳቀች።
መላዕቱም ወደ ሳራ ዞሩ'ና፦"አንችም ኢስሀቅ የተባለን ነቢይ ትወልጃለሽ"
አሏት።
ሳራም በጣም በመገረም አፏን ይዛ፦"ይህ ግን እንዴት ይታሰባል ኢብራሂም
እኮ የጃጀ ሽማግሌ ሲሆን እኔም መሀን ነኝ" ስትላቸው።
መላዕክቱም ምንም እንኳን ሳራ መሀን ብትሆን እና ኢብራሂምም ሽማግሌ
ቢሆንም አላህ ልጅ በቅርቡ እንደሚሰጣቻው እና ያ ልጅም ወደፊት ነቢይ
እንደሚሆንም አክለው አረጋገጡላቸው።
እና መላዕቱም ጉዞ ወደ ሰዶማውያን ጀመሩ።(በነገራችን ላይ ሉጥ
ከኢብራሂም ከተለያየ በኋላ ሰዶም ወደተባለ ሀገር በመሄድ ዳዕዋ ማድረግ
ጀምሯል።ይህን ደሞ ነገ ምንዳስሰው ይሆናል።)
አሁን ነፍሰ ጡሯ የኢብራሂም ሁለተኛ ሚስት ወንድ ልጅን ተገላግላለች።ይህን
ግዜ በሳራ የቅናት መንፈስ ያድርባትና ኢብራሂምን የተወለደለትን አዲሱን ልጅ
እና አዲሲቷን ሚስቱን ራቅ ወዳለ በረሀ ጥሏቸው እንዲመጣ አዘዘችው።
ኢብራሂምም ሚስቱን ሀጀርን እና ልጁን ኢስማዒልን ይዞ ጉዞ ወደ በረሀ
ጀመረ።ብዙ ከተጓዙ በኋላም በዐረብያ ምድር ምንም ውሀም ይሁን አረንጓዴ
ነገር ከሌለበት አንድ ተራ ደረሱ።
የያዘውንም ስንቅ አስቀምጦላቻው ኢብራሂም ወደ መጣበት ሲመለስ ሚስቱ
ሀጀር፦'በዚህ በረሀ ትተኸን እየሄድክ ነው? ወይስ አላህ አዞሀል?" አለችው
እሱም፦"አዎ" ብሏት ጉዞ ቀጠለ።
ትንሽ ሄድ አለ'ና፦"ጌታችን ሆይ! እኔ አዝመራ በሌለው ሸለቆ ውስጥ
በተከበረው ቤት አጠገብ ከዘሮቼ አስቀመጥኩ፡፡ ጌታችን ሆይ! ሶላትን
ያቋቁሙ ዘንድ (አስቀመጥኳቸው)፡፡ ከሰዎችም ልቦችን ወደእነሱ የሚናፍቁ
አድርግ፡፡ ያመሰግኑህም ዘንድ ከፍሬዎች ስጣቸው፡፡" ብሎ ዱዓ አደረገ'ና
ወደመጣበት ለመመለስ ጉዞ ጀመረ።
ብዙ ተጉዞ ሚስቱ ሳራ ወዳለችበት አካባቢም ሲደርስ ሚስቱ ወንድ ልጅ ታቅፋ
አገኛት በጣምም ተደሰተ።
ያችኛዋ ሚስቱ ምንም እንኳን አየሩ ለመቋቋም በሚያዳግት መልኩ ሞቃታማ
ቢሆንም የያዘችውም ውሀ ቢያልቅም በህይወት ግን ከልጇ ጋር እስካሁን
አለች። ውሀ ጥም አንገብግቧታል... ምንም የቀመሰችው ነገር ባለመኖሩ ልጇ
ከጡቷ ምንም ሊያገኝ አልቻለም።
ህፃኑ ኢስማዒል ረሀቡን መቋቋም አቅቶት በጣም እያመረረ ማልቀስ
ጀምሯል...ሀጀርም ምን ማድረግ እንዳለባት ግራ ገብቷት ትተክዛለች።
አየሩ በጣም ሞቀታማ ነው፣ፀሀይዋ ሙሉ ብርታቷን በዛ ምድር ምታሳርፍ ነው
ሚመስለው...መሬቱ ግሏል...ነገር ግን ምንም አማራጭ የላትምና ውሀ
ፍለጋ ልጇን አስቀምጣ በበረሀው ለመሯሯጥ ወሰነች።
ከብዙ ፍለጋ በኋላ ውሀ ልታገኝ ባለመቻሏ ያለ ውሀ ህፃኗ ጋር መመለስ
አልፈለገችም'ና ከአንዱ ተራራ ወደ አንዱ ስትሸጋገር ሰፋ እና መርዋ በተባሉ
ሁለት ተራራዎች ዘንድ ደረሰች በመሀከላቸው ትልቅ ሸለቆ አለ።
ከዚያ ሀጀር ውሀ ይኖራል ብላ እየሮጠች ወደ ሰፋ ተራራ ወጣች ምንም
የለም።
አሁንም ወደ ሸለቆው ወርዳ ወደ መርዋ ተራራ እየሮጠች ወጣች ነገር ግን
አይደለም ውሀ ይቅርና እርጥበት እንኳን የለም።
በዚህ ሁኔታ ከሰፋ ተራራ ወደ መርዋ ተራራ ለ7 ግዜ ውሀ ፍለጋ በሩጫ
ተመላለሰች።
አሁን ሀጀር ድካሟን መቋቋም ባማትችለው ሁኔታ ላይ ደርሳለች፣ጉሮሮዋ
ደርቋል፣ ዳግም ውሀ ፍለጋ ተራራዎችን መውጣት ተሳናት።
ከዚህ በላይ ከቆየች ልጇ እንዳይሞትባት ስለሰጋች ልጇን ወዳስቀመጠችበት
ድንኳን አቀናች።ልክ ህፃኑ ጋር ስትደርስ ህፃኑ እያለቀሰ ሲፈራገጥ በእግሩ
መሬቱን ሲደበድብ ከመሬቱ ውሀ ሲወጣ ተመለከተች።
ደስታዋ ወደር አጣ ውሀውን ጠጥታ ልጇን አጥብታ ለጌታው ምስጋናዋን
አደረሰች።በዚህ ሁኔታ ላይ ሳለች መንገደኛ ነጋዴዎች በውሀ ጥም ተቃጥለው
ያንን በረሀ ሲያቋርጡ ይህን ምንጭ ይመለከቱ'ና ሀጀርን አንድ ግዜ ከፍለዋት
ሊጠጡ ለመኗት።
እሷም ከውሀው ፈቅዳላቸው በአፀፋው ተምር ተቀበለቻቸው.....እነሱም
ጠጥተው አለፉ
እንዲህ እንዲህ እያለ በውሀ ችግር የሚታወቀው የዐረብያ ምድር በሀጀር
ምንጭ ወሬው ተጥለቀለቀ የተለያዩ የዐረብ ነገዶችም ከሀጀር አቅራቢያ
እየሰፈሩ ግንባታዎችን መገንባት ጀመሩ።
ከረጅም ግዜ በኋላም ኢብራሂም ልጁን ኢስማዒልን እና ሚስቱን ሀጀርን ከምን
እንደደረሱ ለማጣራት ያስቀመጣቸው ቦታ ሲመጣ ቦታውን ሊያውቅ
አልቻለም።
ምክንያቱም ያኔ ሲመጣ አከባቢው ምንም አይነት ነፍስ ያለው ነገር
የማይኖርበት ምድረ በዳ ነበር።አሁን ግን ቤቶች ተገንብተዋል...የብዙ ተጓዥ
ነጋዴዎችም ማረፊያ ከተማ ሆኗል።
ይህን ሲያይ መንገድ ተሳስቼ ይሁን እያለ ያሰላስል ጀመር።በዚህ ሁኔታ ላይ ሳለ
የአከባቢውን ሰው ሀጀር ስለምትባል ሴት ሲጠይቁት ከነ ቤቷ ጠቆሙት።
ኢብራሂምም ቤቷ ሲሄድ በጥሩ ሁኔታ ላይ ከልጇ ጋር ተመለከታት...እንባ
ተናነቀው...ሁለቱንም ለረጅም ሰዐት አቀፏቸው ያለቅስም ጀመር።
ከዚያ በዚህ ሁኔታ ከተገናኙ በኋላ ኢብራሂም ወደ መጣበት ተመለሰ።ምንም
እንኳን የልጁ ኢስማዒል እና የሚስቱ ፍቅር እንደ አዲስ በውስጡ ማንሰራራት
ቢጀምርም በመሀከላቸው ካለው ርቀት አንፃር በፈለገ ሰዐት እየመጣ
ሊዘይራቸው ምቹ አልነበረም'ና ሁሌ በአመት አመት ሊያያቸው መምጣት
ጀምሯል።
ከእለታት አንድ ቀን ኢብራሂም ተኝቶ ሳለ በህልሙ፦"ኢብራሂም ሆይ! አላህ
ልጅን ኢስማዒልን እንድታርደው አዞሀል" የሚል ድምፅ ሰማ'ና ደንግጦ ተነሳ።
ከዚያም፦"ጌታዬ ኢስማዒልን እንዳርደው ምትፈልግ እንደሆን ታዛዥህ ነኝ"
ብሎ ተመልሶ ተኛ።
አሁንም እንቅልፍ ትንሽ ሸለብ እንዳደረገው፦"ኢብራሂም ሆይ! አላህ ልጅህ
ኢስማዒልን እንድታርደው አዞሀል" የሚል ድምፅ በህልሙ ተሰማው። አሁንም
ደንግጦ ተነሳ'ና ረክዐተይን ሰግዶ አላህ ትዕዛዙን ግልፅ እንዲያደርግለት ዱዓ
አድርጎ ተመልሶ ተኛ።
አሁንም ልክ እንደተኛ ለሶተኛ ግዜ፦" ኢብራሂም ሆይ! አላህ ልጅህ
ኢስማዒልን እንድታርደው አዞሀል" የሚል ድምፅ ሲሰማ ኢብራሂም ለጌታው
ታዛዥ ሆኖ ከተኛበት ተነሳ።የጌታው ትዕዛዝ ምንም እንኳን ለህሊና ሚከብድ
ቢሆንም ኢብራሂም ሊፈፅም ወሰነ።
ኢብራሂምም ትዕዛዙን ሊፈፅም ጉዞ ኢስማዒል እና ሀጀር ወደሚገኙባት ቅድስት
ከተማ መካ ሄደ።ልክ እንደደረስ ኢስማዒልን ብቻውን ሊያናግረው ወጣ
አድርጎ፦"ልጄ አንተን እንዳርድህ ጌታዬ አዞኛል ምን ትላለህ!?" አለው።
ኢስማዒል፦"ዞር በል ከዚህ..
ስንት አመት ጥለኸኝ የትም የትም ብዬ ካደግኩ በኋ...