Get Mystery Box with random crypto!

የደራሲያን ቤት 123@🇪🇹 የድሮ ሙዚቃዎች 📷📸

የቴሌግራም ቻናል አርማ yederasiyanbet — የደራሲያን ቤት 123@🇪🇹 የድሮ ሙዚቃዎች 📷📸
የቴሌግራም ቻናል አርማ yederasiyanbet — የደራሲያን ቤት 123@🇪🇹 የድሮ ሙዚቃዎች 📷📸
የሰርጥ አድራሻ: @yederasiyanbet
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.91K
የሰርጥ መግለጫ

➕ሁሉም ባንድ ላይ ➕
✔የህወት ታሪኮች
✔የፍቅር ገጠመኞች
✔ምክሮች
✔ ግጥሞች
ይገኝበታል⚫

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-09 21:22:35
ጨዋታው በኢትዮጵያ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

ኢትዮጵያ ግብጽን በአስደማሚ ሁኔታ 2 ለ0 አሸንፋለች!!

ለአፍሪቃ ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ የምድብ ግጥሚያውን ሐሙስ፤ ሰኔ 2 ቀን፣ 2014 ዓም ማላዊ ቢንጉ ብሔራዊ ስታዲየም ውስጥ ያካኼደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የግብጽ አቻውን 2 ለ0 አሸንፏል።

ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ግብ በ21ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው ዳዋ ሆቴሳ ነው። ሁለተኛውን ግብ ደግሞ በ40ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ ያሳረፈው ሽመልስ በቀለ ነው። ሁለቱም ግቦች የኢትዮጵያ አጥቂዎች ድንቅ ብቃት የታየበት ነው።

እንኳን ደስ አላችሁ፣ አለን
3.8K viewslife, 18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 11:27:15 በጎዳና ላይ ካገኘዋቸው የኔ ቢጤ አባት ጋ ያደረኩት የሦስተኛው ቀን ንግግር ክፍል 12

ከብዙ ዝምታ በኋላ እንዴ አሉ አዲሱ አባት ቀና ብዬ ሁለቱን አባት ስመለከታቸው ከኔ ጀርባ የሆነ ነገር እያዩ እንደሆነ ተረዳሁ። አስተያዬታቸውን ሲያዩዋቸው በጣም የተገረሙ ይመስላሉ ፊታቸው ላይ የደስታ ይሁን የድንጋጤ የማይለይ ስሜት ይነበብባቸዋል። ምን አይተው ነው ይሄን ያህል ብዬ እኔም ላይ ዞር ስል ምንም አይነት ነገር የለም ምን አስበው ነው ብዬ ዞር ብዬ ሳያቸው ሁለቱም ፈገግ አሉና አይዞህ የኔ ልጅ ትንሽ እናዝናናህ ብለን ነው አሉኝ።

እናንተማ የፊልም አርቲስት ብትሆኑ ያዋጣችሁ ነበር ብዬ በሆዴ ፈገግ አልኩኝ። የፈረዋቸው አባት እንደሚታዩት አይደሉም ንፁህና የዋህ ይመስላሉ ብዙ ጊዜ ሰዎችን በሩቅ አይተን የምንሰጠው ግምት ፍፁም ስህተት እንደሆነ እሄው በመረጃ እያዬሁ ነው። ሁለቱ አባቶች አፍ ለአፍ ገጥመው ማውራት ጀመሩ ሲያወሩ ላያቸው ከአንድ የእናት ማህፀን የተወለዱ ይመስላሉ። መወለድ ቋንቋ ነው የሚለውን በሁለቱ አየሁ ፍቅራቸው መተሰሳሰባቸው የሌለ ደስ ይላል።

ሁለቱ እያወሩ እያለ ጠጋ ብዬ ቁጭ አልኩኝ ሁለቱም በአንድነት ወደ እኔ ተመለከቱኝና ያወሩኝ ጀመር። እኔ እምፈራቸው አባት የህይወት ገጠመኘን የሰሙ ይመስላሉ ብቻ ሁለቱም የሚያሳዩኝ ፍቅር የተለየ ነው እሽ ብለውኝ አብሪያቸው መኖር ብችል ምንኛ ደስ ባለኝ ግን እሄን አይፈልጉም እርስ በራሳቸውም ለምን አብረው እንደማይኖሩ የገባኝም ቆይቶ ነበር። አስተሳሰባቸው ከሰው ልጆች ወጣ ያለና እንቁ አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎች ናቸው።

አይ አንቺ ሃገር የሚገነባሽንና የሚያፈርስሽን ለይተሽ የማታቂ የሰው ውሻ የሆንሽ ሃገር ብዬ እርር አልኩኝ። ስሜቴን አንብበውት ነው መሰል የኔ ልጅ ዛሬ ለቅሶ የለም አሉኝና ንግግራቸውን ሊቀጥሉ ሲሉ ሁለቱንም እንዲህ ስል ጠየኳቸው።

ለምን ግን ኢትዮጵያ ልጆቿን እንደ በግ ትሰዋለች ለምን? ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርጋት እንቁ እንቁ አዕምሮ ያላቸውን ልጆቿን በሙሉ ያሉት ወይ በአብያተ ገዳማት ነው አልያ ደግሞ ሳያብድ ያበዱ መስለው እብድ እየተባሉ ልክ እንደናንተ እየኖሩ ነው ከነዚህም የተረፈት ምድር ቤት ተዘግቶባቸዋል አልኳቸውና እምባዬን ማዝረክረክ ያዝኩኝ። እዚች ሃገር ላይ የነገሰው ህዝብን ከህዝብ የሚያባላ ሆዳም ባለስልጣን ለራሱ ጥቅም የሚሮጥ የወረቀት እውቀት ብቻ የያዘ ከንቱ ትውል ነው እያልኩ ሳነባ የምፈራቸው አባት በቃ በቃ የኔ ልጅ አሉኝና ዝም አሉ። ሁለቱ አባቶች አይን ለአይን ሲተያዩ ቆዩና እንዲህ አሉኝ።

የኔ ልጅ ጥሩ አስተውለሃል አደራህን ሁልጊዜም የነገሮችን ሁሉ ምላሽ ፍቅር አድርገው ሲሉኝ መስማማቴን ለመግለጽ አናቴን ነቀነኩኝ። አሁን ልብ ብለህ አዳምጠኝ አሉኝ የምፈራቸው አባት እሽ አልኩኝና አይን አይናቸውን ማየት ጀመርኩ የገረመኝ ነገር ያኛውም አባትም እንደ እኔ ንግግራቸውን ለመስማት የጓጉ መምሰላቸው ነው። ወይ ጉድ ብዬ ተገረምኩ እውቀት ያለው ሰው እውቀትን ለማግኘት በአገኘው አጋጣሚ ሁሉ እንደሚያነብና ሰወችን እንደሚያዳምጥ ከኒህ አባት ተረዳሁ።

የምፈራቸው አባት ንግግራቸውን እንዲህ ሲሉ ጀመሩ ልጄ ስትኖር ሦስት አይነት ሰዎችን አክብር
የእውቀት ባለቤቶችን
ቤተሰብህንና አዛውንቶችን በህይወትህ ስትኖር ደግሞ ሶስት ነገሮች ይኑሩህ ታማኝነት እምነትና መልካም ስራ
ራስህን ደግሞ ከሦስት ነገሮች አርቅ
ሰዎችን ከመናቅ
ከማጭበርበር
ከብድር
ሦስት ነገሮችን ተቆጣጠር
ምላስህን
ቁጣህንና ስሜትህብ አሉኝና ትኩር ብለው ተመለከቱኝ ያሉኝን በደንብ እየተከታተልኳቸው መሆኑን ሲገባቸው አሁንም ንግግራቸውን ቀጠሉ። ልጅ ከሦስት ነገሮች ራስህን ጠብቅ
ከመጥፎ ስራ
ሰዎችን ከማማት
ከምቀኝነት
ሦስት ነገሮችን ደግሞ ፈልግ
እውቀትን
ጥሩ ስነምግባር እና ታዛዥነትን
በህይወትህ ስትኖር ደግሞ ሦስት ነገሮችን አስታውስ
መጀመሪያ ሞትን ቀጣይ ደግሞ ሰዎች የዋሉልህን ውለታ እና ሰዎች የሰጡህን ምክር አሉኝና ፀጥ አሉ። እኔም ንግግራቸው በጣም ገርሞኝ ስለነበረ በራሴ ሃሳብ ገብቼ ፀጥ አልኩኝ ሰው እንዲህ በቀላል ቃላት በቀላል አረፍተ ነገር ሰውን መምከር ይገርማል አቤት ተሰጥዖ ብዬ እየተገረምኩ ብዙ ዝም ካልኩኝና

ከብዙ ዝምታ በኋላ ሁለቱ አባቶች እርስ በርሳቸው መነጋገር ጀመሩ እኔም ፀጥ ብዬ ማዳመጥ ጀመርኩ። የሰው ልጆች እሴት መሆን ያለበት እውነትን እንዲጋፈጡና ስድስተኛው የስሜት ህዋሳቸውን እንዲጠቀሙ ማድረግ ነው። ስድስተኛው የስሜት ህዋሳቸው ከሌላ የሚመጡ የማይታወቁ ቃላትን ለማወቅ ይረዳቸዋል። እያሉ ንግግራቸውን ቀጠሉ።

እኔን እረስተውኛል መሰል እያልኩ አንድ ባንድ ንግግራቸውን መስማት ቀጠልኩ። ሰዎች ለልጆቻቸው ማስተማር ያለባቸው ስለ ችግሮች እና ችግሮችን እንዴት ማለፍ እንዳለባቸው ነው። የእያንዳንዱ ችግር መፍትሄ ያለው ችግሩ ከተፈጠረበት ሁኔታ ብዙም ባለመራቅ እንደሆነ መንገር ይጠበቅባቸዋል።

ልጆች ሁልጊዜም ቢሆን መርሳት የሌለባለው አንድ ነገር ቢኖር ውስንነታቸው የሚመነጨው እነርሱ እራሳቸው በውስጣቸው ላይ በሚፈጥሩት ውስንነት አልያ ደግሞ ሌሎች አዕምሯቸውን ውስን እንዲሆን በፈቀደላቸው ልክ ነው። ሁልጊዜም ልጆች በውስጣቸው ያሰቡትን ማድረግ እንደሚችሉ ማወቅ አለባቸው። እውቀት ከምስጋና ሲጀምር አልችልምን ገድሎ ያሰቡትን በማድረግ የሚተካ የአለም ሰላም ነው እያሉ ንግግራቸውን ቀጠሉ።

የነዚህ ሰዎች ንግግር በጣም ገረመኝ የሆነ ሰዓት ያነበብኩት መፅሐፍ ትዝ አለኝና ልፋ ያለህ ፀሃፊ አልኩኝ እሱ በስንት ልፋት ያሳተመውን መፅሐፍ እሄው በቀላል ነገር እኒህ አባቶች ይተነትኑታል። መፅሃፍ በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈና ብዙ ጊዜ የታተመ መፅሐፍ ሲሆን እርዕሱ The secret of humanity እሚል መፅሔት ነበር ግን እኒህ ሰዎች የመፅሐፍ ፀሐፊ አስተማሪ ይመስላሉ።

የሁለቱ አባቶች ንግግር ሲታይ ማቆሚያ ያለው አይመስልም ስለ አለም ይተነትኑ ጀመር። በመሃል ጣልቃ ገባሁና አንድ ጥያቄ አለኝ አልኳቸው ሁለቱም ወደ እኔ ዞር ሲሉ ሲመስለኝ ሁለታችሁም አንድ አይነት እውቀት አላችሁ ቅር የማይልዎ ከሆነ ስለ እራስዎ ቢነግሩኝ አልኳቸው እብድ የሚመስሉትን አባት የጠየኩበት ዋናው አላማዬ እንዴት ይሄን ያህል እወቀት ተምረዋል አልተማሩም የሚለውን ለመለየት ፈልጌ ነበር።

ፈገግ አሉና ይሁና አሉኝና እንዲህ ሲሉ ንግግራቸውን ቀጠሉ አሁን እድሜየ ከ80በላይ ነው አሉኝና በትዝታ ስምጥ አሉ ወዲያው ፊታቸው ቅይርይር አለ የተከፉ ይመስላሉ አይናቸው ላይ የእምባ ጠብታ ሳይ አንጀቴ ስፍስፍ አለ አምባዬን ማቆም አቃተኝ አይናቸውን እብስ አደረጉና እንዲህ ሲሉ ንግግራቸውን ቀጠሉ...
ክፍል13...ይቀጥላል



@yederasiyanbet
4.3K viewslife, 08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 11:23:54 ልጩህበት !

#ክፍል_አስራ_ሶስት


ተነስተህ በቦክስ ወደ ጀርባው ዘርረውና ልጅቷን ይዘኃት ውጣ ውጣ አለኝ።
መሲ ተነስታ ወደ ሽንት ቤት ስትሄድ ከጀርባ ተከተልኳት ! እሷ ከፊት እኔ ከኋላ ወደ ሽንት ቤት እምትወስደው ቀጭን መንገድ መሀል ላይ እንደደረስን ከጀርብዬ ኮቴ ሳያሰማ ማጅራቴ አከባቢ •••
ኮሌታዬን ቀብ ሲያደርገኝ በድንጋጤ መንጭቄው በፍጥነት ዞርኩ!
"ክክክ አንተ ምነው ? ሊያጠቃኝ ይችላል ብለህ የምታስበው ጠላት አለህ እንዴ?
ተፈናጠርክ እኮ ካካካ•••!"

ኮንትራት የያዘኝ ሰውዬ ነበር። የሚገርመው እራሴ አምጥቼው ሳበቃ እዛ ጭፈራ ቤት የውስጠኛው ክፍል ውስጥ መኖሩን ጭራሽ ረስቼዋለሁ!
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት ጎን ለጎን እየሄድን •••
"ደሞ ደክሞኛል ገብቼ ተኛለሁ ባጃጅ ከፈለክ ብለህ ሌላ ስልክ ሰጥተከኝ አልነበር እንዴ የሄድከው ነው ወይስ ሞባይሉን ሰጠኸኝ ስትወጣ አንዷ ጠልፋህ ነው? መሆን አለበት ! እዚ ቤት ያሉ ሴቶች እኮ ልዩ ናቸው እንኳን
እዚህ ድረስ እራሱ የመጣውን ሰው በአየር ላይ ፖይለቱን አማሎ አውሮፕላን ለመጥለፍ ወደኋላ የማይል ውበት ነው ያላቸው ቆይ የጭፈራ ቤቱ ባለቤት የቁንጅና ውድድር አዘጋጅቶ ከአንድ እስከ አምስት የሚወጡትን ነው እንዴ የሚቀጥረው! ካካካ!"
ኧረ መቆለል አልኩና በሆዴ !
ኧረ አይደለም ባጋጣሚ ነው አልኩት ሸንተን ስንመለስ•••
"ምኑ ነው አጋጣሚ ቆንጆዎች መሆናቸው?"
አይ የኔ እዚህ መከሰት!
"እና ብቻህን ነህ ብቻህን ከሆንክ ለምን ውስጥ እኔጋ አለመጣህም " እያለ አቁሞ ሲነዘንዘኝ መሲ ከሽንት ቤት ወጥታ እየተውረገረገች ባጠገባችን አለፈች። አፈጠጥኩባት ።
እሱም በሚስቁት አይኖቹ እኔ ላይ አፈጠጠብኝ ።
"ተመለስክ?!"
ኬት ?
"ከልጅቷ ላይ ነዋ!"
አዎ አልኩት ፈገግ ብዬ !
በል ና እሄንን እማ እየጠጣን ነው መስማት የምፈልገው ናናናና !" እያለ እጄን እንደያዘ ወደ ውስጥ ገባን።
እዛ የተገኘሁበትን እውነት ልንገረው? አልንገው ? ብነግረውስ ምን ብዬ ልንገረው? ምናልባት ጥሬ እውነቱን እንደወረደ ስነግረው ምናልባት እኔን የተሰማኝ ስሜት ካልተሰማው•••
"ቆይ ከልጅቷ ጋር ዘመድ ናችሁ?"
ኧረ አይደለንም ።
"ትውውቅ አላችሁ ማለት ታውቃታለህ ?"
አይ!
"እሺ ቆይ ልጅቷን ወደሀታል?'
ኧረ በጭራሽ!
"ታድያ ምን አግብቶህ ነው እዚህ ሁሉ ፈተና ውስጥ እራስህን የምትከተው?!" ቢለኝስ!
እኔ የሴቶች እህቶቼ ጉዳትና ጥቃት እንደሚያገባኝ አምናለሁ ይሄ የሚያገባቸው የማይመስላቸው እሄን ምን አገባኝ እያሉ ነገር ግን በማያገባቸው ብዙ ነገሮች ውስጥ እጃቸውን የሚያስገቡ ሰዎች በዙርያችን ብዙ ናቸው።
የሴት ጥቃት አይመለከተኝም እያሉ የአርሰናል መጠቃት የሚያደባድባቸው በሞሉባት ሀገራችን
አላውቃትም!
ዝምድናም የለንም!
አልወደድኳትም!
እያልክ ለሷ መቆም እንቆቅልሽ የሚሆንበትና ምን አገባህ የሚልህ ቢያጋጥምህ ምን ይገርማል?!
ምንም!።
ስለዚህ ምን ልበለው? በቀላሉ የሚፋታኝ አይመስለኝም ።
"ምናገባህ!" እንዳይለኝ ትንሽ ቀየር አድርጌ ልነግረው ወሰንኩና•••
ይሄውልህ ቅድም ሞባይሉን ሰጥቼህ ስወጣ የአንደኛ አመት የዩንቨርስቲ ተማሪ የሆነችውን የአክስቴን ልጅ ከማይሆን ሰው ጋር አየኋት!
ከኔ ጋር ከተጣላን አመት ሆኖናል። ተኮራርፈናል። አንነጋገርም ግን ብንጣላም ስለሰውየው በደንብ ስለማውቅ ጥያት በጭራሽ አልገባም ልጅቷ እንደዚህ አይነት አመል የላትም እርግጠኛ ነኝ ቅድም የገላመጥኳት ልጅ በሆነ መንገድ ሸውዳ አምጥታለት ነው •••
አልኩና ስለመሲና ስለሰውየው በዝርዝር ነገርኩት።
እሄን ግዜ ሰውየው ከኔ በላይ የተቆጣ ነብር ሆኖ ቁጭ አለ። ፊቱ ተለዋወጠ።
"በቃ ይሄን ጉዳይ ለኔ ተወው አንተ ዝምበልና ቁጭ ብለህ ጠጣ!"
ማለት ምን ልታደርግ ነው?!
"ዝም ብለህ ጠጣ! ብዬሀለሁ ዝም ብለህ ጠጣ!" አለኝ ክርድድ ባለ ድምፅ።
ድሮም ነገረ ስራው ግራ ነበር የሚገባኝ አሁን ደግሞ ባንዴ ሲለዋወጥብኝ እኔ እራሴ ፈራሁት ።
ካጠገቤ ሄዶ እነመሲን ከሩቁ አይቷቸው ተመለሰ።
ከደቂቃዎች በኋላ ከነመሲ ጋር ያለው ሰውዬ ቦርጩን እያሻሸ ወደ ሽንት ቤት ሲያልፍ እኩል እየነው! ተያየን••ኀ
"እሄ አሁን ያለፈው ነው አደለ?
"አዎ ግን ምን ልታደርግ ነው?
"አቢቲ አማርኛዬ አልገባ ካለህ የፈለከውን የሚገባህን ቋንቋ ንገረኝና በሱ ላስረዳህ ከዚህ በኋላ ለኔ ተወው የትም እንዳትንቀሳቀስ እዚሁ ቁጭ ብለህ እየጠጣህ ጠብቀኝ !"
ብሎኝ ሰውየውን ተከትሎ ወደ ሽንት ቤት ሄደ።
ብዙም ሳይቆይ ተመልሶ መጣና ምንም ሳይለኝ መጠጣት ጀመረ
ወደሽንት ቤት የሄደውን ሰውዬ ካሁን ካሁን ይመለሳል ብዬ ብጠብቅም አልተመለሰም ጨነቀኝ እንዴ ምን አርጎት መጣ? ግራ ገባኝ
ምን አልከው ሰውየው እኮ ብር ያጠገበው ባለጌ ነው ምን አለህ? ስለው•••
መልስ ሳይሰጠኝ እሄን ውስኪ እንደውሃ እየጠጣ •••
"ጠጣ ጠጣ ያቺን አየሀት ዝም ብላ እያየችህ ነው አብረካት መደነስ ትፈልጋለህ ልጥራት እንዴ?"
አለኝ ጥግ ኮርነር ላይ ካሉት ሴቶች መሀል ወደኛ እያየች ወደምትናጠው ሴት እያመለከተኝ
ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?!
ወደ ሽንት ቤት ሌላ ሰው በሄደ እና በወጣ ቁጥር እያየሁ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት እራሴ ሄጄ ለማረጋገጥ ስለፈለኩ•••
••• እሺ መጣሁ አንዴ ስመለስ አብሪያት እደንሳለሁ አልኩትና ሄድኩ መጀመሪያ ወደነመሲ ገልመጥ ሳደርግ ሁለቱ ብቻ ናቸው እነሱም እንደኔ ሰውየው የት ሄደ ብለው ግራ ተጋብተዋል መሰለኝ ግራና ቀኝ ይገላመጣሉ ።
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት በፍጥነት ሄድኩና ከአምስቱ ሽንት ቤቶች መሀከል ክፍት የሆኑትን ሁለቱን አየት አድርጌ በማለፍ ሶስተኛውን ስበረግደው•••

ይቀጥላል...

#ደራሲ_ጥላሁን

@yederasiyanbet
3.2K viewsnothing, 08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 09:48:27 በጎዳና ላይ ካገኘዋቸው የኔ ቢጤ አባት ጋ ያደረኩት የሦስተኛው ቀን ንግግር ክፍል 11

ልክ እንደነጋልኝ ትንሽም ብትሆን ቁርስ መሳይ አስሬ መንገዴን ቀጠልኩ እየሄድኩ እያለ አንድ የጥያቄ ሃሳብ ድርቅ አድርጎኝ ቀረ። ይህን ነበር ያሰብኩት እስከመች ነው ከኒህ አባት ጋር እየሄድኩ እማወራ እሚል ጥያቄ ነበር ሁሌ መሄድ አልችልም ሳልሄድም መዋል አልችልም ግራ ገባኝ በጣም ተወዛገብኩ ምን አይነት ውሳኔ ልወስን አንዱን መምረጥ ግዴታዬ ነው ግን እንዴት እያልኩ እየተውሰነሰንኩ እያለ ከባስ የውረዱ መልክት ክላክስ ሲጮህ ንቅት አልኩኝና ፈጠን ብዬ ከባስ ወርጄ መንገዴን ወደ ተወዳጁ አባት አደረኩ ስደርስ ግን በቦታቸው ላይ አላገኘዋቸውም ነበር።

ከዚህ ቦታ የሚለቁ አይመስለኝም ነበር ዛሬ ግን ከቦታቸው ላይ የሉም ቁጭ ብዬ ልጠብቃቸው ብዬ ከመቀመጫቸው ላይ ቁጭ እንዳልኩኝ ለምን ማስታወሻቸውን ገልጭ አላነበውም አልኩኝ ሌላኛው አዕምሮዬ ደግሞ ፈቃዳቸውን ሳጠይቅ አለኝ ግራ ተጋባሁ ይቅርብኝ ብዬ ቁጭ ብዬ መጠበቁን ያዝኩኝ ከአንድ ሰዓት በላይ ከጠበኳቸው በኋላ ትላንት መተው ካስደነገጡኝ አባታ ጋር እያወሩ ሲመጡ ተመለከትኩኝ።

ትላንት ገልምጠውኝ የሄዱት አባት ዛሬ ሲያዩኝ በደስታና በፈገግታ ነው የሚመለከቱኝ ምን ሆነው ነው ብዬ ግራ ተጋባሁ ትላንት እንደዚያ የገላመጡኝ ሰውዬ ዛሬ ምን ተገኝቶ ነው እንዲህ በፈገግታ የሚያዩኝ እያልኩ ሳምሰለስል አጠገቤ ደርሰው የኔ ልጅ ብለው እየተካኩ እቅፍ አደረጉኝ። ትላንት ገላምጠውኝ የሄዱት አባት ጠረናቸው እውነትም የመንገድ ላይ ነዋሪ ያስመስላቸዋል። ልብሳቸው ከተገዛ ታጥቦ የሚያውቅ አይመስልም ፀጉራቸውም ሰውነታቸውም ክረምት ዝናብ ሲዘንብ ሲመታቸው ካልሆነ በቀር ውሃ ነክቷቸው የሚያውቁ አይመስሉም ግን የደስደስ አላቸው።

እረዘም ያሉ ሲሆነ በዕድሜና በችግር ብዛት ነወው መሰል አጎብድደው ነው የሚሄዱ ብቻ ላያቸው ያሳዝናሉ። ካቀፉኝ በኋላ በአንድ ላይ ተቀመጥ አሉኝ እሽ ብዬ እየፈራሁ ቁጭ አልኩኝ የያዝኩት ቁርስ ለሁለታቸው እንደማይበቃ ስላሰብኩ አንዴ መጣሁ ብዬ ልሄድ ስል ቁጭ በል አሉኝ የምፈራቸው አባት እመለሳለሁ እኮ አልኳቸው ይበቃናል ቁጭ በል አሉኝ ምኑ አልኳቸው ድንግጥ ብዬ ተቀመጥ ፍቅር ካለ አንድ እንጀራ ለብዙዎች በቂ ነው ሲሉኝ ፍዝዝ ብዬ ቀረሁ። እንዴት አወቁ ብዬ በጣም ደነገጥኩ ለመጠየቅ ግን ድፍረቱ ስላልነበረኝ እሽ ብዬ ቁጭ አልኩኝ።

ሁለቱ ከአማረኛ ውጭ በሆነ ቋንቋ ትንሽ ካወሩ በኋላ በመሃላቸው ፀጥታ ሰፈነ ያወሩት ወሬ በግዕዝ እንደነበረ ተረድቻችዋለሁ ግዕዝ ማውራት ባልችልም ትንሽ ትንሽ እሰማለሁ ቅላፄውም አይጠፋኝም። ዝምታቸውን ጨርሰው ሲመለሱ ትንሽ ብትሆንም ይቺን ቁርስ ተካፈሏት አልኳቸው ተባረክ የኔ ልጅ አሉኝና በአንድነት ፀሎት አድርሰው እርስ በርሳቸው ተጎራርሰው በአንድነት ለኔም አጎረሱኝ ፍቅራቸውን ሳይ እምባዬን ማቆም አቅቶኝ ለቀኩት እምፈራቸው አባት ሲያዩኝ አሳዝኛቸው ነው መሰል እምባቸው በሁለቱም ጉንጮቻቸው ይፈሱ ጀመር። በጣም ደነገጥኩ ለካ ወንድ ልጅ ሲያለቅስ ያስደነግጣል እኔ ሁሌ ሳለቅስ ምንም ተሰምቶኝ አያውቅም ነበር እኒህን አባት ሳይ ግን ድንጋጤዬ ከሚገባው በላይ ነበር።

ወዲያው ሁለቶቹ ተቃቀፉና ምን ነው አባቴ ይህማ ደግም አይደል አሏቸው ልክ ብለዋል የልጁ አኳኋን አሳዝኖኝ ነው አሉና ያችን ትንሽዬ ቁርስ እርስ በርሳቸው እየተጎራረሱ ጨረሱ ወዲያው ፀሎት አድርሰው ሁለቱም ወደ እኔ ተቀመጥኩበት ቀርበው ተቀመጡ። ትላንት የገላመጡኝን አባት ዛሬም በጣም እፈራቸዋለሁ ለምን እንደሆነ አላውቅም።

የኔ ልጅ አሉኝ በአንድነት አቤት አባቶቼ አልኩኝ በአግራሞት ከመጡ እስከ አሁን ቃላቶችን በአንድ ላይ ስለሚያወጡ ገርሞኛል አጋጣሚ ይሁን ምን እማቀው ነገር የለም ግን ከአራት ጊዜ በላይ ጠሩኝ ሁለቱም በአንድ ላይ በአንድ ሰዓት ነው የሚጠሩኝ በዚያ እየተገረምኩኝ አሁንም በአንድነት የያዝከውን ማስታወሻ ስጠን እስኪ አሉኝ።

የያዝኩት ማስታወሻ ትላንት ከአዩት ሌላ ማስታወሻና የህይወት ገጠመኘ ስለነበረ ኧረ አይሆንም አልኳቸው ድንግጥ ብዬ። አሁንም በአንድነት ለምን አሉኝ የግል ሚስጥሬ ነው ትላንትም እኮ የሰጠዎት እንዳላስከፋዎ ብዬ ነው አልኳቸው። ዛሬም እኮ ይከፈኛል ካልሰጠኸኝ አሉኝ ይቅር ይበሉኝ አባቴ ልሰጥዎ አልችልም አልኳቸው። እርስ በርስ ከተያዩ በኋላ በአንድነት ትኩር ብለው አዩኝ። አልፈራሁም ግን አኳኳናቸው ደስ አላለኝም ወዲያም ምን እንርዳህ? አሉኝ። ደነገጥኩ ምን ማለታቸው ነው ብዬ ለራሴ እ አልኳቸው ደግመው ምን እንርዳህ? አሉኝ።

ወይ ዛሬ ባልመጣሁ በቀረብኝ ብዬ መምጣቴን ማማረር ያዝኩኝ ማስታወሻዬን መስጠት ደግሞ እንደ ጥሩ ነገር አላየሁትም የፈራሁ አዲስ የመጡትን አባት እንጂ ትላንት እና ከዚያ ቀደም ያገኘዋቸሁ ብቻ አባት ቢሆኑ ኑሮ ባላንገራገርኩ ነበር። ልጄ አሉኝ አሁንም በአንድነት አቤት ብዬ አይን አይናቸውን ማየት ቀጠልኩ አሁንም እንደገና በድጋሚ ምን እንርዳህ? አሉኝ። በለው ብዬ ሃሳብ ከምድር ይገኝ ይመስል መሬት ላይ አፈጠጥኩ።

ሁለቱም አያወሩ በመሃላችን ዝምታ ሰፈነ ምን ብዬ ወሬ እንደማስጀምር እማቀው ነገር የለኝም ብቻ በቃ መነሻ ምክንያት ባገኝ ተመልሼም የማያቸው አይመስለኝም ግን መነሻ ምክንያት አጣሁ። ከብዙ ዝምታ በኋላ እንዴ አሉ አዲሱ አባት ቀና ብዬ ሁለቱን አባት ስመለከታቸው ከኔ ጀርባ የሆነ ነገር እያዩ እንደሆነ ተረዳሁ። አስተያዬታቸውን ሲያዩዋቸው በጣም የተገረሙ ይመስላሉ ፊታቸው ላይ የደስታ ይሁን የድንጋጤ የማይለይ ስሜት የነበብባቸዋል። ምን አይተው ነው ይሄን ያህል ብዬ እኔም ላይ ዞር ስል...
ክፍል12...ይቀጥላል


_ _

#ከወደዱት ለወዳጅ ዘመድዎ share

@yederasiyanbet
3.0K viewslife, 06:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 23:41:51 Meselu fantahun full album
2.6K viewslife, edited  20:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 23:38:12 GiGi full album
2.6K viewslife, edited  20:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 23:31:45 Tamrat desta full album
በአንድ ላይ

@yederasiyanbet
2.6K viewslife, edited  20:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 23:22:46 Mikiya Behailu full album

@yederasiyanbet
2.5K viewslife, edited  20:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 11:11:27 ልጩህበት !

#ክፍል_አስራ_ሁለት

ጭፈራ ቤቱ ውስጠኛው ክፍል ውስጥ ገብቼ ስልኩን ሰጥቼው ልወጣ ሁለት እርምጃ እንደተራመድኩ ድንገት ወደ ቀኝ ገልመጥ ሳደርግ
ሁለት ሴቶችና አንድ የሰፈራችን ሀብታም ነጋዴ የተቀመጡበት ሶፋ ላይ አይኔ ተተክሎ ቀረ።
ደነገጥኩ!
ሰውየው የኤች አይ ቪ ኤድስ ተሻካሚ የሆነና ሚስቱ በዚሁ በሽታ የሞተችበት ሰው ነው ።

•••ሁለቱ ሴቶች ደግሞ አንዷ ጭራቋ ስትሆን አንዷ ደግሞ ምናልባት የነኤዱ ጓደኛ ሳትሆን አትቀርም ወይኔ ቲጂ እንዲህ አንድፍሬ ልጅ ነሽ ቆይ ኧረ •••
አልኩና እየተጣደፍኩ ከጭፈራ ቤቱ በመውጣት ሞባይሌን ከኪሴ አውጥቼ ፎቶ ማህደሩን ከፈትኩ አልተሳሳትኩም መሲ እራሷ ነች ከንፈሮቼን በሶስት ጣቶቼ ተጭኜ የመሲ ፎቶ ላይ እንዳፈጠጥኩ ወደ ባጃጄ ውስጥ ገብቼ ተቀመጥኩ ።
መደበኛ ስራዎ እሄ መሆኑን አውቃለሁ እኔን ያስደነገጠኝ አገር ምድሩ ሚስቱ በምን እንደሞተችና እሱም ምን እንዳለበት ከሚያውቀው ከዚህ ህሊና ቢስ ቀበጥ ጋር መተዋወቋ ነው።
ምንም የማያውቁ ከየቦታው የሚመጡ ፍሬሽ ተማሪዎችን እያቀረበችለት ሲጫወትባቸው ታየኝ እሷና እሱን ከዚህ ውጪ ምንም ሊያገናኛቸው እንደማይችል ግልፅ ነው ።

ሰውየው እንደሆነ ከመጨረሻዋ ልጅ እኩዮች ጋር ለመጋደም ፈሪሀ ህሊንም ሆነ ፈሪሀ ፈጣሪ ያልፈጠረበት አረመኔ መሆኑን እንኳን እኔ በታክሲ ስራ ምክንያት ከተማ ውስጥ ስቅበዘበዝ የምውል ከቤት የማይወጣ የሰፈራችን ሰው ቢኖር እንኳን ስለዚህ ሰውዬ ለመስማት መጠየቅ አይጠበቅበትም ስለሰፈራችን ሀብታሞች ከተወራ የሚወራ ብዙ ነገር ያለው እሱ ነው።
ባጠቃላይ ሰባት ልጆች አሉት። እናት አባቶቻችን ስለሱ ሲያወሩ•••
" ሀብታም የሆነው አንድ ልጁን ለሰይጣን ገብሮ ነውኮ ልጁ መፍዙዝ ሆኖ ግቢያቸው ውስጥ ካለች አንድ ክፍል ውስጥ ጫቱን ሲደፈልቅ ውሎ ነው እሚያድረው ወደውጪ ሳሰማይወጣ ሰው አያውቀውም!" ሲሉ ሰምቻለሁ
ለሀብት ሲል የገዛ ልጁን እንደዛ ያረገ ሰው ደግሞ ለምድር ቆይታው በቀሩት የተገባደዱ ቀሪ እንጥፍጣፊ አመታት የልጁ ታናሽ እና እኩያ የሚሆኑ ሴት እህቶቻችንን በገንዘብ ሀይል ጨርሶ ለማለቅ ባይሽቀዳደም ነበር እሚገርመኝ!።
ምን እንደማደርግ ግራ ገባኝ ስለዚህ ሰው ማንነት እያወኩ ቢሳካም ባይሳካም ልጅቷን ከሱ ለማስጣል ሳልሞክር ወደቤቴ ብሄድ የሰላም እንቅልፍ እንደማይወሰደኝ ምናልባትም እስክረሳው እና ባስታወስኩት ቁጥር የጥፋተኝነት ስሜት እንደሚለበልበኝ አውቀዋለሁ ።

የሆነ ነገር መሞከር አለብኝ አልኩ ለራሴ ሞክሬ ካቅሜ በላይ ሆኖ ባይሳካ እንኳን ከህሊና ክስ እተርፋለሁ!
አካሄዴን ከማጣራት መጀመር እንዳለብኝ አስብኩ ምክንያቱም መሲ የዚህ አገር ልጅ ስለሆነች ዘመዱ ብትሆንስ አብራቸው ያለችው ልጅ ደግሞ የነ ኤዱ ጓደኛ ትግስት ባትሆንስ?
እዛው ባጃጄ ውስጥ እንዳለሁ ኤዱ ጋር ደወልኩ
አነሳችው። ግዜ ሳላጠፋ ቀጥታ ወደገደለው ገባሁ•••
ኤዱ የጓደኛሽን የትግስትን ፎቶ በቴሌግራም ላኪሊኝ
"ለምን ? ምነው? በሰላም ነው?"
አዎ በሰላም ነው አፍጥኚው!
ላከችልኝ። ትግስት ናት ብላ ኤዱ የላከችው ፎቶና አሁን በዚህ ሰአት ከነመሲ ጋር ያለችው ልጅ ጭራሽ አይገናኝም!
ሌላ ነች ማለት ነው? የግቢ ልጅ ትሆን ? በራሴ ጥያቄዎች ስወዛገብ ኤዱ ደወለች•••
ወዬ ኤዱ
"ምንድን ነው እሱ?" አለችኝ ያየሁትን ነገርኳት
"እስቲ የልጅቷን መልክ ንገረን "አለች።
ከረዱ ጋር አብረው እንደሆኑ ገባኝ ምናልባትም ስልኳን ድምፅ ማጉያ ላይ አድርጋው ለሁለት እየሰሙኝ ነው።
የልጅታን መልክ ማብራራቴን ጀመርኩ•••
ልጅቷማ ደስ የሚል ቅጥነት ያላት! ፀጉሯን ብራውን የተቀባች በጣም ቀይ ! አፍንጫዋ •••
እያልኩ ከአናቷ ጀምሬ ቁልቁል ልወርድላት ስል ካንገቷ ሳልሻገር ልጅቷን አወቋት መሰለኝ ቆይ ቆይ አንዴ ቴሌግራም ላይ ገባና ጠብቀኝ ብላ መልሴን ሳትሰማ ስልኩን ጠረቀመችው።
የላከችው ፎቶ ቴሌግራሜ ላይ እንደገባ በፍጥነት በረገድኩት እሚገርመው ልጅቷ እሄን ፎቶ ከለቀቀች ቡሀላ ፎቶው ላይ ያለውን ልብሷን ሳትቀይር ነው ወደጭፈራ ቤቱ የመጣችው ምናልባትም ወደዚህ አምሮባት ስትመጣ ተነስታ ቴሌግራሟ ላይ ለቃው ይሆናል።
ኤዱ እሄን ፎቶ ኬት ነው ያገኘሽው?
"ዛሬ ቀን ዘጠኝ ሰአት አከባቢ ነው የፌስ ቡክ ፕሮፋይል ፒክቸሯን የቀየረችው ከዛ ላይ እስክሪን ሹት አድርጌ ነው የላኩልህ ምነው ልጅቷ እራሷ ነች እንዴ ዳንዬ!?
አዎ እሷ ናት ስላቸው ሁለቱም ጮሁ!!
ምንድን ነው ምንሆናችሁ ኤዱ?
ቆይ እሷ ትንገርህ እንቺ ብላ ስልኩን ለረድኤት ሰጠቻት •••
" መሲ በመጨረሻም ተሳክቶላት እቺን ልጅ ወጥመዷ ውስጥ ጣለቻት እኔ አላምንም! "
ማለት? አልኳት።
ግራ ገብቶኝ አንቺ ኤዱ እና ትግስትስ በወጥመዷ ውስጥ ገብታችሁ የለ እንዴ
የሚለውን ሀሳብ ለራሴ እያወራሁት ቀጠለች•••
"አንድ ቀን ልጅቷ ባጠገባችን ስታልፍ መሲ ልጅቷን በክፉ አይን ስታያት አየሁና ምነው? ስላት•••
እቺ ልጅ ለጓደኛዋ ድንግል ነኝ የጀመርኩት ነገር የለም ማለቷን ሰምቼ ላጠምዳት ብሞክርም ገገማ አሳ ሆነችብኝ!።
ጋደኛዋ በኔ ቀመር እየተሽቀረቀረች ልታስቀናት ብትሞክርም ልጅቷ አልሞቅ አልደንቅ እንዳላት ነገረችኝ አሁን ሳያት ታስጠላኛለች !
" ብላ ስትነግረኝ •••
ምነው የኔ አይን አርፎባት! ለሆነ ቢዝነስ አቀባብያት ! ሳልተኩሳት የምትክሽፍብኝ ሴት የለችም ስትይ አልነበር እንዴ ታድያ እቺ እንዴት ከሸፈችብሽ ? ስላት
ኮሚሽን ሼር ሳላደርግ ለብቻዬ ማጣጣም ስለፈለኩ እንጂ እኔ መሲ እልህ ውስጥ ከገባሁ የትኛዎም የግቢ ሴት በዘረጋሁላት መረብ ላይ መወዘፏ የማይቀር ነው! "
ኮሚሽን ሼር ላለማረግ ስትል ምን ለማለት ፈልጋ እንደሆነ ጠየኳት እንዲህ አለች•••
እቺ ልጅ ጋደኛዋ ብትሽቀረቀር ብትብለጨለጭ ብልጭ አይልባትም አደል ስለዚህ እቺን በብልጭልጭ ነገር ማጥመድ አይቻልም ለእንደዚህ አይነት ሴቴች ደግሞ እቅድ ሁለት (ፕላን ቢን) እጠቀማለሁ የቱንም ፈተና ብትቋቋም ያንን መቋቋም ይከብዳታል።
እንደዚች አይነቷን በሴት ሳይሆን በወንድ ታጠምጃታለሽ እንኳን የሷን የድንጋይን ልብ የሚያቀልጥ ስንት የድሬ ልጅ ሞልቷል እሄን ያህል እከፍልሀለሁ በግር በጇ ብለህ አጥምዳት ብለው ሁለት ሳምንት ባልሞላ ግዜ ውስጥ አምጣት ያልኩት ቦታ እያክለፈለፈ ያመጣልኛል ግን ከልጅቷ ሽያጭ ግማሹ የሱ ነው ያንን ነው ኮሚሽን ያልኩሽ ብላኝ ነበር ይገርማል በዛ መንገድ ሸውዳ እጇ አስገባቻት ማለት ነው!?"
ስትለኝ እልህ አንቀጠቀጠኝ !
በፍፁም አታስገባትም! ኡልኩና ስልኩን ዘጋሁባት!
ምናልባት ሰውየው በአይን ሊያውቀኝ ስለሚችል ባጃጄ ውስጥ ያለውን ጥቁር ኮፍያ አደረኩና እስከ ግንባሬ ዝቅ አድርጌ አጎበጥኩት !
ሰተት ብዬ ወደ ጭፈራ ቤቱ ገባሁና ከነሱ ትይዩ ኮርነር ላይ ተቀምጬ መጠጥ አዘዝኩ።
መሀላቸው ጎልተው ግራ እንዳጋቧት የሚቅበዘበዘው ፊቷ ይመስክራል ። ምናልባቷ አጥምዶ ያስረከባት ልጅ መጣሁ ብሎ በመውጣት በዛው ቀርቶባት ይሆን አስሬ ዘወር ዘወር እያለች እምታየው? አንጀቴን በላችኝ !!
እየጠጣሁ ሁለቱን አውሬዎች ባየኋቸው ቁጥር ንዴቴ እየጨመረ መጣ!
ሰውየው ያንን በድሜ ብዛት ቶሎ ቶሎ ኩበት እየሆነ የሚያስቸግረውን ከንፈሩን በምራቁ ለማውዛት እየመጠጠ ያቺን አንድ ፍሬ ልጅ ለማሽኮርመም ሲታገል ስመለከተው አለም አስጠላችኝ !
ተነስተህ በባክስ ወደ ጀርባው ዘርረውና ልጅቷን ይዘካት ውጣ ውጣ አለኝ።
መሲ ተነስታ ወደ ሽንት ቤት ስትሄድ ከጀርባ ተከተልኳት ! እሷ bከፊት እኔ ከውኋላ ወደ ሽንት ቤት እምትወስደው ቀጭና መንገድ መሀል ላይ እንደደረስን


@yederasiyanbet
7.8K viewsnothing, edited  08:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 12:03:58 በጎዳና ላይ ካገኘዋቸው የኔ ቢጤ አባት ጋ ያደረኩት ንግግር ክፍል 10

ጥያቄዬን እንዲህ ስል ጀመርኩ ቆይ እኔን ለምንድንነው እንደዚያ ያዬኝ አስተያዬታቸው በጣም ያስፈራል ነበር እኮ የተለዬ ምክንያት አላቸው ወይስ አልኳቸው። ሲመጡ ያወሩህ ይሆናል ካላወሩህም እኔው እነግርሃለሁ ሲሉኝ ችኩል ብዬ ምን አለበት ዛሬ ቢነግሩኝ አልኳቸው።

የኔ ልጅ ብዙ ማወቅ ከፈለክ ብዙ አትፍጠን የመጀመሪያውን ሲሰጡህ በመጀመሪያው ተደስተህ መጨረሻውን ሳታይ አትሂድ የረጋ ነገር ሁሉ የረጋ ነገር ያገኛል። ሀ,ሁ ብዬ ብነግርህ ህ,ሆ ብዬ ላልቋጭልህ እችላሉሁና አሳቸውን ጠብቅ አሉኝ። እሽ አባቴ ብዬ እስኪ ስለ እራስዎ በደንብ ይንገሩኝ እዚህ መኖር እንዴት ነው? መቼም እዚህ ሲኖሩ ብዙ ገጠመኝ አጋጥመወት ይሆናል እስኪ ስለገጠመወት ገጠመኝ ይንገሩኝ አልኳቸው።

ገጠመኜ ይገርማል እዚህ ስኖር አንዳንዱ በርግጫ አንዳንዱ በድንጋይ የገጠቅጠኝ ነበር አንዱ ደግሞ ቆሻሻ ውሃ እያመጣ ይደፋብኝ ነበር። እኔ ግን መልሴ ዝምታና ሳቅ ስለነበረ አሁን ሁሉም ሰለቸው መሰል ምንም አያደርገኝ። የሰው ልጅ ስለበላ ስለጠጣ ስለተወደደ ሳይሆን መኖር የሚችለው መኖር ስላለበት ነው። የኔ ልጅ እኔ እዚህ ስኖር አመንክም አላመንክም ምግብ ሳልበላ ለሰባት ቀን ቆይቼ አውቃለሁ በርግጥ ሳይንሱ አንድ የሰው ልጅ ከአስራ አምስት ቀን በላይ ያለ ምግብ መቆየት ይችላል ነው የሚል የኔ ግን የሚለየው ያለ ውሃ ጭምር መሆኑ ነበር እንደ ሳይንሱ አንድ የሰው ልጅ ያለ ውሃ ያለ ምግብ ለሰባት ቀን መቆየት የማይቻል ነው ነው የሚለው እኔ ግን እንደ ፈጣሪ ፈቃድ ሆኖ ምንም ሳልሆን ቀረሁ እያሉ ሲነግሩኝ ሌቤ በሃዘን አርር አለች።

የኔ ልጅ እንዳንተ ብዙ ፈተና ብዙ መከራ አሳልፊያለሁ ማለት አልችልም ግን ትልቁ ነገር በዚህ ደስታ ቢርቅህ ደስታህ በዘላለም ቤትህ ታገኘዋለህ የሰው ልጅ በምድር ሲኖር ደስታ ሲያጣና መከራ ሲደራረብበት አቤቱ አምላኬ ሆይ ምን በድየህ ነው እንደዚህ የምትፈትነኝ በቃ በላኝ እባክህ እያለ ይለምናል የኔ ልጅ ይህ ስህተት ነው አምላክ ሁሌም ለልጆቹ መልካም ነገር ነው የሚያስቀምጥ ሁልጊዜ የሚፈተኑት በምድር መከራ ያገኙት በዘላለም ቤት አምላካቸው ያስባቸዋል ሲሉኝ ቀበል አድርጌ እንዴ ችግር መከራ የማይደረስባቸውንስ ማለቴ ባለ ሃብተ ዝነኛ ሰዎች የዘላለም ቤት አያገኙም ሊሉኝ ባልሆነ አልኳቸዎ።

የኔ ልጅ እንደሱ ማለቴ አይደለም የሰው ልጅ መከራ ሲያገኘው ፈጣሪን ማማረር የለበትም ነው ለማለት የፈለኩት ሁሌም በተሰጠህ ነገር መመስገን ስትጀምር የሌለህን ትሰጣለህ። ፈጣሪህ ያለህን ሁሉ እሱ ነውና የሰጠህ ያለህን ሲነጥቅህ ማማረር የለብህም ነው ለማት የፈለኩት አሉኝ። ገባኝ ብዬ ንግግራቸውን መስማቱን ቀጠልኩ ንግግራቸው የባሰ እየከረረ መጣ ውስጤን ይነከዋል የሚያወሩት ከልባቸው ነው እዉነት ታፍና ቆይታ ስትወራና ስትሰማ እንደምትከነክንና ውስጥን እንደምትሸረካክት ዛሬ ነው የተረዳሁ።

ንግግራቸው ከልብ ስለነበረ የተለመደው እምባዬ እየፈሰሰ ነበር እኔን ሲያዩ ልባቸው ተነክቶ ነው መሰል በቃ ይብቃህ ልጅ ዛሬ መሽቷል ነገ ስራ ከሌለህ ነገ እናወራለን አሉኝ። በርግጥ ሰዓቱ መሽቷል እንደማያሳድሩኝም ስለማቅ ተሰናብቻቸው ጉዞየን ወደ ቤቴ አደረኩ። እቤት እስከምደርስ ድረስ ስለ እሳቸውና ስለ አለም እያውጠነጠንኩ ነበር የደረስኩት።

እንደተለየዋቸው በምሽቱ ነፋስ በሰዎች ጫጫታ በመኪናወች ግርግር ሳልረበሽ በራሴው መንገድ ከምሽቱ ድባብ ጋር እያወራሁ መንገዴን ቀጠልኩ። የሰው ልጆች ስንባል ከንቱወች ነን አላማ አለን ግን አላማችንን አናቅም። ባለ ሃብት ዝነኛ መሆን እንፈልጋለን ነገር ግን ሃብትም ዝናም ተኝተን እሱ በራችንን እንዲያንኳኳ ነው የምንፈልገው። አዕምሯችን ገደብ የሌለው ጥልቅ ውቅያኖስ ሆኖ እያለ አጥበን የጉድጓድ ውሃ እናደርገዋለን።

ስንፈጠር ሁሉን እንድንችል ሁሉን እንድናደርግ ተደርገን ነው የተፈጠርን ነገር ግን አልችልም የሚል የስንፍና ቃል እያወጣን የምንችለውን በአልችልም ተክተን ደካሞች እንሆናለን። እንደ እኒህ ሰውየ ፍልስፍና ከሆነ ህይወትን ከባድ ያደረግናት እኛ ነን። ከሳቸው እይታ ተነስቼ እኔም ስለ ትምህርት እንዲህ ስል አሰብኩ ሲጀመር ትምህርት እየተባልን የምንማረው ትምህርት የመጥበባችን የመጀመሪያው ምክንያት ነው።

ትምህርት ትምህርት ሊባል የሚችለው ሁሉም በብቃቱ ሲማር ነበር። እኛ ግን ሁላችንም የምንማረው ትምህርት አንድ አይነት ነው ይህ ስህተት ነው። የሰው ልጅ ሲፈጠር የተለያዬ መልክ የተለያዬ አረማመድ የተለያዬ ስብዕና የተለያዬ አነጋገር እንዳለው ሁሉ የተለያዬ አስተሳሰብና ብቃትም አለው። እርግጥ ነው ስንፈጠር ሙያ ይዘን አንወለድም ግን ከሰው ለየት የሚያደርገን ነገር ይዘን ነው የምንፈጠረው።

ትምህርት ማለት ያንን ከሰው ለየት የሚያደርገንን ብቃትና ልዩ ተሰጦ ለይቶ ማሳወቅ እንጂ መሆን የነበረበት የማያውቁትን የውጭ ቋንቋ መሸምደድ አልነበረም መሆን የነበረበት። በኢትዮጵያ የሰው ልጅ ትልቁ ውድቀቱ ትምህርት ነው እኛ ሃገር ላይ የራሳችንን ታሪክ እንኳን የምንማረው የውጭ ዜጋ የፃፈውን ነው። ኢትዮጵያ ማደግ ካለባትና አንድ መሆን ካለብን ወይም የሙህሮች ሙህር መሆን ከፈለግን ትምህርትን እንደገና ሀ ብለን መጀመር ይኖርብናል።

የውጭ ዜጎች እኛን በነሱ የትምህርት ካሪክለም እያደነነዘዙ በጎን የኛን ቋንቋ እያጠኑ የሃገራችንን እንቁ መፅሐፍ እየዘረፉ ይከብሩና ይደልቁብናል። በኛ ነገር ላይ የሰሩትን አዲስ ስራ እንደሰሩ እራሳቸውን እየካቡ ለኛ ይሸጡልናል። እኛ ኢትዮጵያውያን ዝም ብለን እየለፋን አሜን እንላለን የገንዛ ገንዘባችንን በገንዛ ገንዘባችን እንገዛለን። ይች ሃገር የሃገሮች ሃገር መሆን ከፈለገች የትምህርት ካሪክለምን ወደ እኛ መቀየር ይኖርብናል እንደገና መጀመር ይኖርብናል ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ሌሎች ሃገሮች የሉም ሁሉም የማደጋቸው ምስጥር ኢትዮጵያ ነች እኛ ግን ይህን አናቅም ብናውቅም መለየት አቅቶናል። የአወቅን መስሎን ሳናውቅ ብዙ እየሄድን ነው። ብልጦች የኛን የሃገራችንን ሚስጥር እንዳንፈታ አዕምሯችንን በነሱ የትምህርት ካሪክለም እያደነዘዙ እነሱ በጎን ሃገር ይዘርፋሉ።

ትምህርት ስንጀምር ከሀ -ሆ ከቆጠርን በኋላ አ,ቡ,ጌ,ዳ...ሆ,ሳ,ብ,ዕ ብለን ፊደል ቆጥረን ሁለተኛም ስራችን የኛን ብቃት መለየት በቀጣይ በየ ብቃታችን መሰማራት እንጂ በማይታወቅ የውጭ ዜጋ በተፃፈና የኛን አዕምሮ ለማደንዘዝ በተሰራ የትምህርት መወጠርና መውደቅ ያለብን አይመስለኝም። የኛ ችግራችን አላማ ያለው በትምህርት ብቻ ነው አድርገን የምንቆጥረው እውነቱ ግን ትምህርት ብለን የምንማረው ትምህርት የመጀመሪያው የጭንቅላታችን ማደንዘዣ መርዝ ነው እያልኩ በሃዘን እየተንገበገብኩ እያሰብኩ እያለ ከጎኔ የሆነ ድምፅ ቀሰቀሰኝ።

ሳይታወቀኝ ያ ልማደኛ እምባዬ እየፈሰሰ ኑሯል ምነ ነው ደህና አይደለህም ችግር አለ አለችኝ ከጎኔ የጠቀመጠች አንድ ሴትዮ ኧረ ደህና ነኝ ብዬ እምባየን አባብሸ መንገዴን ቀጠልኩ። ሰፈር ስደርስ ከታክሲ ወርጄ ነገ የምጠይቃቸውንና ምን እንደሚሉኝ ማሰብ ጀመርኩ
የስወስተኛው ቀን ንግግራችን ክፍል 11 ይቀጥላል
ክፍል11...ይቀጥላል



@yederasiyanbet
3.1K viewslife, 09:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ