╔═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╗ ." ከራስ ሽሽት ". . ( ሶፊያ አህመድ ) ╚═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╝ . በ @tibebislam_nw የቀረበ . ልብ አንጠልጣይ ታሪክ .━─━────༺༻────━─━ #ክፍል_አምስት. . .⓹ ❦•⊰❂⊱• ════ ❦ ሀሰን እስከ ምሽት 5 ሰአት ድረስ የሀዩን የስልክ ጥሪ እየጠበቀ የስልኩ ስክሪን ላይ አፍጥጧል። መሀል መሀል ላይ እንቅልፍ እያዳፋው ከስልኩ ጋር ሲጋጭ ብድግ ይልና ፊቱን በውሀ አርሶ መልሶ ይቀመጣል። የእሷን ስልክ ምን ያህል በጉጉት እየጠበቀ እንደሆነ ብታውቅ ኖሮ ምናልባት ለመደወል ደቂቃዎችን ባላባከነች ነበር። በህይወታችን ምዕራፍ ውስጥ ስለኛ ደስታ ብለው እኛ ሳናውቀው በድብቅ ብዙ ዋጋ የሚከፍሉልን ሰዎች ይኖራሉ። አንዳንዴ ግን እኛ ለነሱ የምንሰጠው ምላሽ በተቃራኒው ሲሆን እጅግ ያማል! ሀሰን ከሁለት አመት በላይ በሀዩ ፍቅር መሰቃየቱ ፣ በናፍቆት ተቃጥሎ ህመሙን ለሌላ ሰው አለማሰማቱን ከራሱና ከአላህ ውጪ ማንም አያውቀውም። እንደሌሎቹ ወንዶች ፍቅሩን ገልፆ ሀዩን የራሱ ሊያደርጋት የሚችልበት ድፍረት የለውም። ይሄንን ባህሪውንም የተረዳችው ሀዩ ብቻ ነበረች። ግን እሷም ዛሬ ከልቡ እንጂ ከእይታው ጠፍታ ስቃይ ሆናበታለች። በእያንዳንዱ ዱዓው መሀል አላህን ሁዩን እንዲሰጠው ሳይለምነው ቀርቶ አያውቅም። ፅናቱ ፣ ተስፋ አለመቁረጡ ከምንም በላይ ጀግንነቱን ያሳያል! ሀዩ ጋር ስላለው ስሜት ፈፅሞ አያውቅም፤ ግን እሱ ጋር የሷ ፍቅር ልቡን ሞልቶታል። በቃ ተስፋው አላህና ፍቅሩ ብቻ ናቸው! በፊት የነበረው ዝምተኝነት ተፈጥሮአዊ ቢሆንም ሀዩን ካጣት በኋላ ግን እየባሰ መምጣቱ ቤተሰቦቹን በጣም አስጨንቋቸዋል። እሱን ለማስደሰት ምንም ነገር ቢያረጉለትም የሱ ባህሪ ግን ሊቀየር አልቻለም። ደስታውን ሀዩ ስትሄድ አብራ ይዛው ሳትሄድ አትቀርም። ሀዩ እንቅልፍ እንቢ ሲላት ፈቲን ቀስቅሳ ልታማክራት አሰበች። ግን ፈቲ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ስለወሰዳት ልትሰማት አልቻለችም። ለሀሰን ለትደውልለት ስልኳን ታነሳና መልሳ ደሞ ታስቀምጠዋለች። ለምን መደወል እንደፈራች ግልፅ ነው። በዚ ሰዓት ጊዜዋን መስጠት የምትፈልገው ለቤተሰቦቿ ብቻ ነው። ከዚ በኋላም ሀሳቧን እንዳትቀይር ሀሰን የሰጣትን ደብዳቤ ከነስልክ ቁጥሩ ቀዳዳ ጣለችው። አበቃ! ጠዋት ሀዩ በጊዜ ስለምትነሳ ሁሉንም ቀስቅሳ የሱብሂን ሰላት በጋራ ሰገዱ። አባታቸው አቶ ጀማል አንድ ስልክ ተወድሎላቸው ለማውራት ወጡ። ልክ አናግረው እንደተመለሱ