Get Mystery Box with random crypto!

የ ፍቅር ጥግ

የቴሌግራም ቻናል አርማ ye_dessie_lijoci — የ ፍቅር ጥግ
የቴሌግራም ቻናል አርማ ye_dessie_lijoci — የ ፍቅር ጥግ
የሰርጥ አድራሻ: @ye_dessie_lijoci
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 467
የሰርጥ መግለጫ

‼️DESSIE‼️

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-30 17:37:34 የዘንድሮ 12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ጣጣ !

800ሺ በላይ ተፈታኝ :

በዘንድሮ አመት ከ1 ሚሊዮን በላይ በማታ በቀን እና በግል እንዲሁም አምና የወደቁ የአማራ እና ሌሎይ ክልል ተፈታኞች አጠቃላይ ከ1ሚሊዮን በላይ ብሄራዊ ፈተናን የሚወስዱ ተፈታኞች አሉ ። ከእነዚህ ውስጥ አጠቃላይ የዮኒቨርስቲዎች የመቀበል አቅም ከ200ሺ በፍፁም አይዘልም ይሄም ከ4 ተፈታኝ አንድ ሰው ብቻ የዮኒቨርስቲን ደጃፍ እንዲቀላቀል ያስገድዳል። ፎክክሩ እጅጉን በጣም ከባድ የሞት ምድብ ነው ። ታዲያ ከእነዚህ ውስጥ እርሶ ብቁ መሆንን አይሹም

Online ፈተና

ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመርያ ግዜ የ12ተኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በOnline ለመተፈን እየጣረች ነው እውንም የሚሆን ይመስላል ። አስባችሁታል አንብብባችሁ ነገር ግን በቴክኖሎጂ አዲስነት ምክንያት ውጤታችሁ ሲበላሽ ሞባይል ምን እንደሆነ የማያውቁ በርካታ የገጠር ተማሪዎች ያሉበት ሀገር ነው ያለነው ።

በዮኒቨርስቲዎች የሚሰጥ ፈተና

በድጋሚ ኢትዮጵያ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ብሄራዊ ተፈታኞችን በዮኒቨርስቲዎች እንደምትፈትን ገልጣለች ይሄም ተማሪዎች በማያውቁት ሀገር እና Environment ውስጥ እንዲፈተኑ ያስገድዳል ይሄም ተማሪዎችን ለስነልቦና ጫን ያጋልጣቸዋል ። ቢያንስ 3 ቀን አከባቢውን መለማመጃ ጊዜ ሊሰጣቸው ይገባል ብለን እናምናለን !

ከ9-12 የሚያጠቃልል ፈተና

ላለፉት 20 አመታት ድረስ ቀርቶ የነበረው እና በ1994 የቆመው የትምህርት ፓሊሲ የተመለሰ ይመስላል ተማሪዎች ብሄራዊ ፈተናን ከ9ኛ ክፍል እስከ 12 አጠቃለው እንደሚፈተኑ ተነግሯል ፈተናውም 70% ከ12 እና 11 ክፍል 30% ደሞ ከ9-12 እንደሚያጠቃልል ሰምተናል ። ይሄም ተማሪዎችን የበለጠ ጫና ውስጥ ይከታል



https://t.me/ye_dessie_lijoci
140 viewsedited  14:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 17:30:56 በባሕር ዳር ከተማ የባጃጅ ወይም የባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ እስከ ምሽቱ 2:00 ብቻ እንዲኾን ተገደበ፡፡

ባሕር ዳር: ሰኔ 23/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ፀጥታ ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ምክር ቤቱ በአደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የሕዝብን ሰላምና ደኅንነት የሚያስጠብቁ ውሳኔዎችን ማሳለፉን አስታውቋል።

ከተወሰኑ ልዩ ልዩ መሠረታዊ ውሳኔዎች መካከል ደግሞ የመጀመሪያው የባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴን ይመለከታል ብሏል።

ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው አሁን ካለንበት ሀገራዊ እና ክልላዊ ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር ለከተማው ሰላምና ደኅንነት ሲባል ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ማንኛውም የባጃጅ ወይም የባለሦስት እግር ተሽከርካሪ እስከ ምሽቱ 2:00 ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ይሆናል። ከምሽቱ ሁለት ሰዓት በኋላ ሲንቀሳቀስ የተገኘ ማንኛውም የባጃጅ ተሽከርካሪ ላይ ለሚወሰድበት ማንኛውም ቅጣትና እርምጃ ኀላፊነቱን ባለቤቱ ወይም አሽከርካሪው ይወስዳል ነው ያለው።

ማንኛውንም ወንጀል መከላከል የሚቻለው የኅብረተሰብ ተሳትፎ የላቀ ሲኾን መኾኑን የገለጸው ምክር ቤቱ የከተማው ነዋሪ እንደተለመደው ጥቆማዎችን በመስጠትና ከሕግ አስከባሪዎች ጎን በመቆም ለሰላም ዘብ እንዲቆም ጥሪ አቅርቧል፡፡
ምክር ቤቱ "በፀጥታ ኀይላችን ብርቱ ትግል፣ በሕዝባችን የማይቋረጥ ደጀንነት የአፍራሽ ኀይሎች ምኞት አይሳካም " ብሏል፡፡
መረጃው የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ነው፡፡
151 views14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 08:53:48 #የሱዳን_ጦር_ኃይሎች "ስለ ሱዳን መከላከያ ሰራዊት የተሰራጩ ዜናዎች የእኛ አይደሉም" ሲል ገለፀ!!!

"በተለያዩ የዜና አውታሮች #በአልፋሽቃ በሱዳን ጦር ኃይሎች እና በኢትዮጵያ ወታደሮች ቤተሰቦች ላይ ከሱዳን ጦር እና ወታደራዊ ምንጮች ጋር የተያያዙ ሰበር ዜናዎች የተሳሳቱ ናቸው።

" በማለት ማምሻውን ላይ ባወጣው መግለጫው ያስታወቀው የሱዳን ጦር ኃይሎች ቃል አቀባይ ፅ/ቤት፤ "ድንበራችን ላይ ካለው ሁኔታ ጋር በተያያዘ የሱዳን መከላከያ ሰራዊት ዛሬ ለየትኛውም ሚዲያ የሰጠነው ምንም አይነት መግለጫ የለም።" ብሏል።

በመጨረሻ ላይም ፅህፈት ቤቱ "የሱዳን መከላከያ ሰራዊት ዜና ማሰራጫ ብቸኛ ህጋዊ ምንጭ በመሆኑ ማንኛውንም የሚዲያ ይዘት ለሌላ ምንጭ መጠቀም ከአውጪው ሃላፊነት እና ከህግ ጭምር የሚያያዝ ይሆናል።
" ሲል ገልጿል።
152 views05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 08:53:48 #ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ
የደራ ህዝብ ጦርነት ላይ ነው ያለው !
ኦነግ ሸኔ ወደ ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ የተወሰኑ ቀበሌዎች በመግባት ከህዝቡ ጋር እየተዋጋ ይገኛል ። ባገኘሁት መረጃ መሰረት ሸኔን እየተዋጉ ያሉት የአካባቢው ሚሊሻዎች ብቻ ናቸው ። ከዚያ ውጭ የተላከላቸው የመከላከያም ሆነ የክልል ልዩ ሀይል የለም ።

ጦርነቱ ሞቅ ቀዝቀዝ እያለ ቀጥሏል ። ሸኔ በአሁኑ ሰአት ባቡ እና ራቾ በተሰኙ የደራ ቀበሌዎች ከትሞ ይገኛል ።

ኦነግ ሸኔ በገባባቸው ቀበሌዎች በሙሉ መሳሪያ እየለቀመ ነው ። አብዛኛው የደራ ህዝብ መሳሪያ ታጣቂ እንደመሆኑ ከገበሬው ብቻ የሚሰበስበው መሳሪያ ትልቅ ግብአት የሚሆነው ነው ።
ሸኔ ወደ ደራ ዋና ከተማ ጉንዶመስቀል ለመግባት የሚያደርገው ጥረት በሚሊሻዎቹ ተጋድሎ ሲመከት ቢቆይም በአሁኑ ሰአት ሸኔ ወደ ወረዳው ያስገባው ሀይል በርካታ በመሆኑ ሚሊሻዎቹ አሸባሪውን ቡድን ከወረዳው ጨርሶ ማባረር አልተቻላቸውም ።

አሁን ራቾና ባቡ በተሰኙት ቀበሌዎች የአርሶአደሩን በሬዎች እያረደ እየበላ ይገኛል ። ንፁሀንንም አግቶ ይዟል ። የገበሬውን ምርትም ከየጎተራው እየሰበሰበ ለቀለቡ የሚሆነውን እያከማቸ ይገኛል ።
መንግስት ለደራ ህዝብ ተገቢውን ትኩረት እንዲሰጥ ጥሪያችንን እናቀርባለን
141 views05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 08:53:48 ቆቦ
በራያ ቆቦ በ036 መንጀሎ ቀበሌ በአንድ ፖል ላይ የተጠቀለለ ባለ 10 ሜትር ኦፒቲካል ፋይቨር ገመድ ማንነታቸው ባልታወቀ ግለሰቦች( ቡድኖች) በመዘረፉ ምክንያት በቀን 21-10-2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ከ08 አራዶም ቀበሌ ጀምሮ ቆቦ ከተማን በጨምር የስልክ እና የባንክ አገልግሎት የተቋረጠ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን።
ነገር ግን በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያ የሚወራው የሃሰት ፕሮፓጋንዳ መሆኑን እንድትገነዘቡ እያሳሰብን፤አዲስ ነገር ካለ የምናሳውቅ ይሆናል።
የራያ ቆቦ ኮምንኬሽን
129 views05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 08:53:48 #መረጃ!

# በባህር ዳር የአማራ ፋኖ አመራር አባላት የታሰሩት ዘመኔ ካሴን እንዲያሸማግሉ ከተጠየቁ ቦኃላ ነው!!

በባህር ዳር የአማራ ፋኖ አመራር አባላት የታሰሩበትን ሁኔታ አስመልክቶ፣ የአማራ ህዝባዊ ኃይል አመራር አባል የሆነው ጠበቀቃ አስረስ ማረ የሚከተለውን ማብራሪያ ሰጥቷል:-

( በባህር ዳር የአማራ ፋኖ አመራር አባላት እስርን አስመልክቶ) ፋኖ እንዴት ከተማ ሊገኝ ይችላል? የሚል ጥያቄ ሲነሳ አይቻለሁ።

ከፊሉ የዚህ ጥያቄ ባለቤት የእለት ስንቅ ማቀበል የማይችል ተቺ ቢሆንም፣ ጥያቄዉን መመለስ ግን ተገቢ ስለሆነ፣ ያለኝን መረጃ ላካፍላችሁ።

በአጣራሁት መሰረት፣ የባህርዳር ፋኖዎች የአፈና ዘመቻው የተጀመረ አካባቢ ከከተማ ወጥተው ነበር። ሆኖም፣ የከተማዋ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊው ኮ/ር አትንኩት እና የሰላም እና ደህንነት መምሪያ ኃላፊው አቶ አደራውን ጨምሮ ሌሎች የፀጥታ አመራሮች በሰው በኩል ካገኟቸው በኋላ፣ "... መንግስት እናንተን ማሰር አይፈልግም፣ ከቻላችሁ እነ ዘመነን ከመንግስት ጋር የማግባባት ስራ እንዲሰራ አግዙን..." የሚሉ እና ሌሎችም ሃሳቦች አቅርበውላቸው ነበር።

እነሱም ማለት የሚገባቸዉን ተናግረው ለግማሽ ቀን ውይይት ካደረጉ በኋላ ነበር ከጫካ ወደ ከተማ የተመለሱት።
134 views05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 00:46:31
168 views21:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 00:46:30
158 views21:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 07:01:17
#እኔም#የምኒልክ ዘማች ነኝ!!

ከሰሞኑን የአራት ወር ህፃናት ላይ ቢላ የሚያሳርፉ የዓለማችን ፋሪዎች "#ዘመቻ ምኒልክ" የሚለውን ብራንድ ሲወንጅሉ ተመልክቻለሁ። ባትደክሙ ይሻላል። እንዲያውም አንድ እውነት ልንገራችሁ..?

#የኢትዮጵያ ችግር አሁን ላይ የሚፈታው
#በዘመቻምኒልክ፣ #በዘመቻቴዎድሮስ፣ #በዘመቻበላይዘለቀ# እና #በዘመቻአሳምነው ብቻ ነው።

#አገር እየፈረሰ እና ወገን እየረገፈ በየመሸታ ቤቱ የምትርመጠመጥ ሁላ ወየውልህ።#ተነስ፤! #ተደራጀ#ሰልጥን#ታጠቅ! ስትጨርስ "#ዘመቻ ምኒልክን ተቀላቀል።አበቃ!!

#ድልለፋኖ
#ድልለኢትዮጵያ
#እኔም
209 views04:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 07:00:36 ከዓለም አቀፍ የዐማራ ጉባኤ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠ መግጫ!

ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊያንን ጠብቆ ያኖረው የዐማራ ሕዝብ በተለይ ከትህነግ መምጣት ጀመሮ ሲጨፈጨፍ ሲሳደድ የዘር ማጥፋትና ማፅዳት ሲካሄድበት ቆይቷል። አሁንም የሰሞኑ ጭፍጨፋ ማረጋገጫ ነው። ደግሞ የዐብይ አገዛዝ የዘር ማጥፋትና ማፅዳት ወንጀሎችን ለመስቆም እየሰራ እንዳልሆ እኛ በዓለም ዙሪያ የምንገኝ አማራዎች ይህን ግልጽም-ስውርም ደባ በዝምታ ማለፍ የጥፋት ተባባሪነት ስለሚሆን በተናጠል የምናደርገውን የዐማራ የህልውና ትግል በተቀናጀ ስልታዊ መንገድ ለማካሄድ መሰረት የጣልንበት የመጀመሪያው የዓለም አቀፍ የዐማራ ጉባኤ እኤአ በሰኔ 18 ቀን 2022 እና 19 ቀን 2022 አካሂደናል።

በዚህ ጉባኤ የዐማራን ዘር ማጥፋትና ማፅዳት በጽኑ አውግዘን ከዚህ ጋር በተያያዘ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ውሳኔዎች አሳልፈናል።

፩. ጉበኤው እየተካሄድ እያለ ጊምቢ በሚባል የወለጋ በግምት እስከ 2000 የሚደርሱ ዐማራች በመጨፍጨፋቸዉ በጥልቅ የተሰማንን ሃዘን በመግለፅ፣ የተደረገውን የዘር ማጥፋት ወንጀል በጥብቅ በማውገዝ፣ ጉባኤው የ“ኦሮሚያ” ገዢ ሽመልስ አብዲሳ እና ጠቅላይ ሚንስትር ተብዬው አብይ አሕመድ በዘር ማጥፋትና ማፅዳት ወንጀል በህግ መጠየቅ አለባቸው እንጠይቃለን።

፪. “እኔም ፋኖ ነኝ” በሚለው መርሆ መሰረት ፋኖነንትን ማዕከል ያደረገ ሁለገብ የትግል ስልት መቀየስና ለዐማራ ህዝብ ህልውና ከሚታገሉ ሃይሎች ጋር የጠበቀ ግንኙነት መፍጠር አማራጭ የሌለው የትግል ስልት እንደሆነ ወስነናል። ይህንን የወሰንነው የዐማራውን የትግል አቅጣጫ የሚመራ፣ የተለያዩ የዐማራ ማህበራትን ያካተተ የፖለቲካ ማዕከል አስፈላጊ እንደሆነ በመገንዘብ ነው።

፫. በዐማራ ላይ ያነጣጠሩ ብዥታ ፈጣሪ የውጭ እና የውስጥ የሃሰት ትርክቶችን ለመናድና ትክክለኛውን የአማራና የኢትዮጵያ ታሪክ መርምሮ የሚያሳውቅና የዛሬውን የነፃነት ትግል አቅጣጫ የሚያስይዝ ምሁራዊ የጥናት ቡድን አስፈላጊነትን ተገንዝበን ቡድኑ እንዲስማራ ወስነናል።

፬. በዐማራው ላይ በጦርነት፣ በፓለቲካ፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ለሚደርሱበት ጉዳቶች አስፈላጊውን ሰብአዊ እርዳታ ለማሰባሰብ የተለያዩ የአማራ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ግልጽ በሆነና ተጠያቂነት ባለው መንገድ እንዲሠሩ ወስነናል።

፭. የሰላማዊው ትግል ዘርፍ የፋኖን ትግል መንፈስና እሴቶች በሚያንጽባርቅ መልክ በዉጭ አገር የሚኖሩ ዐማሮችና አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ በቆራጥነት ዐብይ አገዛዝ ተቋማት ላይ የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ አድማ በትብብር ይደረግበት ዘንድ ጉባኤው ጥሪ ያደርጋል።
168 views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ