Get Mystery Box with random crypto!

በቅርቡ በከተማ አስተዳደሩ በተደረገው የትምህርት ቤት አመራሮች ውድድር ወደ ርዕሰ መምህርነት ለመጡ | Addis Ababa Education Bureau

በቅርቡ በከተማ አስተዳደሩ በተደረገው የትምህርት ቤት አመራሮች ውድድር ወደ ርዕሰ መምህርነት ለመጡ የትምህርት ቤት አመራሮች የሚሰጠው ስልጠና ዛሬም እንደቀጠለ ነው፡፡

(ቀን ጥር 29/2016 ዓ.ም) በስልጠናው የሶስተኛ ቀን ውሎ ለትምህርት ቤት አመራሮቹ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጡ ምሁራን በትምህርት አመራር (instructional leadership) ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰቱዋል ።

ስልጠናው ወደ አመራርነት እንደ አዲስ ለመጡትም ሆነ ቀደም ሲል በርዕሰ መምህርነት ሲያገለግሉ ለቆዩ አመራሮች ከትምህርት አመራር ጋር በተገናኘ በቂ ግንዛቤ ጨብጠው በተመደቡባቸው ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ስራውን በአግባቡ መምራት እንዲችሉ ታስቦ መሰጠቱን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የመምህራንና የትምህርት አመራር ዳይሬክቶሬት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ስልጠናው ለተከታታይ ስድስት ቀናት የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮችን መሰረት አድርጎ የሚሰጥ መሆኑን ቀደም ሲል መገለጹ ይታወቃል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc