Get Mystery Box with random crypto!

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ _____________ ፈተናው ከነሀሴ 23 | Wuhalek Ethiopian Construction Talk Show. 0941431700

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
_____________
ፈተናው ከነሀሴ 23 - 27/2014 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን የፈተና ፕሮግራሙም እንደሚከተለው ይሆናል፡-
ፋርማሲ፣ አንስቴዥያ እና ሜዲካል ራዲዮሎጂ ቴክኖሎጂ----------------- 23/12/2014 ዓ.ም
ነርሲንግ --------------------------------- 24/12/2014 ዓ.ም
ህክምና እና ጤና መኮንን ------------- 25/12/2014 ዓ.ም
ሚድዋይፈሪ፣ ዴንታል ሜድስን እና ኢንቫይሮመንታል ሄልዝ ------------- 26/12/2014 ዓ.ም
ሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ፣ ፔዲያትሪክ ነርሲንግ እና ሳይካትሪ ነርሲንግ---- 27/12/2014 ዓ.ም
ተመዛኞች ነሀሴ 22/2014 ዓ.ም ከቀኑ በ 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል እንዲሁም የመፈተኛ ክፍላችሁን መለየት ይኖርባችኋል፣
በፈተናው ዕለት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ (የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድ ወይም ሌላ በግልጽ የሚታይ ህጋዊ መታወቂያ)፣ የፈተና መስሪያ ግብዓቶች (እርሳስ፣ ላጲስ፣ መቅረጫ) እና ስትመዘገቡ ሲስተሙ የሰጣችሁን ስሊኘ ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፣
ከላይ ከተጠቀሱት ነገሮች ውጪ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ ስማርት ሰዓት፣
ኤሌክትሮኒክስ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎች እንዲሁም ባዶ ወረቀቶች፣ ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፣
በፈተናው ወቅት ተመዛኞች በሁለቱም ክፍለ ጊዜ (ጠዋት እና ከሰዓት በኋላ) አቴንዳንስ ላይ በአግባቡ መፈረም ይኖርባቸዋል፣
የመፈተኛ ከተማ አዲስ አበባ የመረጣችሁ ተመዛኞች በአዲስ አበባ ከተማ ከተዘጋጁ አምስት /5/ የፈተና ማዕከላት በአንዱ፣ ሀዋሳ የመረጣችሁ ተመዛኞች በሀዋሳ ከተማ ከተዘጋጁ ሁለት /2/ ማዕከላት በአንዱ እንዲሁም አምቦ የመረጣችሁ ተመዛኞች በአምቦ ከተማ ከተዘጋጁ ሁለት /2/ ማዕከላት በአንዱ የተመደባችሁ ሲሆን ከዚህ በታች በቀረበው የማስፈንጠሪያ ዝርዝር ላይ የተመደባችሁበትን የፈተና ማዕከል መመልከት ይኖርባችኋል፡፡
ከአዲስ አበባ ውጪ ያሉ የመፈተኛ ከተሞችን የመረጣችሁ ተመዛኞች በመረጣችሁት ከተማ ፈተናው የሚሰጥበትን የፈተና ማዕከል ከታች ካለው ዝርዝር ላይ መመልከት ይኖርባችኋል፡፡
የመፈተኛ ከተሞችና ማዕከላት፡
አዳማ …………………………… ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ (አዳማ ካምፓስ)
አሰላ……………………………… አርሲ ዩኒቨርሲቲ
አሶሳ ……………………………… አሶሳ ዩኒቨርሲቲ
አምቦ……………………………… አምቦ ዩኒቨርሲቲ & ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ (አምቦ ካምፓስ)
ባህር ዳር ………………………… ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ
ደብረ ማርቆስ …………………. ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
ደሴ…………………………………ወሎ ዩኒቨርሲቲ
ሐረር ……………………………… ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ (ሀረር ጤና ሳይንስ ካምፓስ)
ሀዋሳ ……………………………… ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ & ሀዋሳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ
ጅማ ……………………………… ጅማ ዩኒቨርሲቲ
ባሌ ጎባ…………………………… መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ
መቱ ……………………………… መቱ ዩኒቨርሲቲ
ጎንደር …………………………… ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
አርባ ምንጭ…………………… አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
ወልቂጤ ………………………… ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ
አዲስ አበባ፣ ሀዋሳ እና አምቦ ከተሞችን የመረጣችሁ ተመዛኞች ከላይ የተያያዘውን ማስፈንጠሪያ በመጫን የተመደባችሁበትን የፈተና ማዕከል መመልከት ትችላላችሁ፡፡
አዲስ አበባ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተመዛኞች የፈተና ማዕከሉ አፍንጮ በር 3ተኛ ፖሊስ ጣቢያ አካባቢ ተስፋሁን ህንፃ ላይ ይገኛል፡፡
አዲስ አበባ:
https://t.me/ayuzehabesha