2022-01-21 22:17:43
ባልወድሽ ነው እንጂ...
ባልወድሽ ነው እንጂ ባላስብሽ እንጂ ብወድሽ ኖሮማ፣
ቤት ሰራልሽ ነበር በሰማይ ከተማ፣
በታላቂቱ ሃገር በገብርኤሏ ራማ።
.
.
.
የሰማይ ፈጣሪ ብርሃን ይኹን ብሎ ብርሃን ባረገበት፣
አቆምሽ ነበረ ጸሐይ ባለችበት።
.
.
.
በጨረቃ ሸራ በነጩ ቀለም ላይ፣
እስልሽ ነበረ ዓለም ኹሉ እንዲያይ።
.
.
.
እልሻለሁ ግና እልሻለሁ ግና ብወድሽ ኑሮማ፣
ከመነኩሴ ሃገር ከገዳሙ ማማ፣
ትታይ ነበረ በሞገስ በግርማ።
.
.
.
እኔ ካፈቀርኩሽ ተራራው ይናዳል፣
ዳሽን ይፈርስና ቀይ ምንጣፍ ተነጥፎ መንገድ ይሆንሻል፣
ጣናም ይደርቅና ተረማመጂብኝ ብሎ ይጠራሻል፣
አክሱም ይወድቅና እንደ ድልድይ ሆኖ ያገለግልሻል፣
ዶፍ እንዳይወርድብሽ የጎንደሩ ፋሲል ዘብ ይቆምልሻል፣
ብወድሽ ኑሮማ እንኳን ሃገር ቀርቶ ዓለም ይበጅሻል፣
የምድሪቱ ሴቶች ቆንጆ ናት እያሉ ይተርኩልሻል፣
የሹማምንት ወንዶች የኔ ትሁን ሲሉ ደም ይቃቡልሻል፣
ታላላቅ ነገስታት ወደ ትቢያ ወድቀው ጫማ ያስሩልሻል ።
.
.
.
እንዲያው ተንሳፈፊ በሃሳብም ሒጂ፣
ብወድሽ መልካም ነው አልወድሽም እንጂ።
ተጻፈ በበረከት ለማ
ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
የፍቅር ጠማቂ
ደመግቡ ሆነሽ ተስለሽ አማላይ
የፍቅር ጠማቂ አዳምን አስኮብላይ
ትናፍቂኝ ጀምር ብውል አንችን ሳላይ ፤
ተጫዋች ነሽ አሉ መስለምለም ምታዉቂ
አንዴ ብቻ ሳይሆን ሁለቴ ምትደምቂ
ልብሽን ደብቀሽ ለሁሉ ምስቂ ።
መረብሽ ምንድነው ቃላውጪ ማሪቱ
አኩኩሉ ሩጬ ከበቆሎ እሽቱ
ጨዋታን ስጫወቱ መዃሸት ኹሸቱ
ልጅነት መሄዱን ሳልይዘው መጥፋቱ
እድሜዬ ነገረኝ አንችን በመሻቱ ።
ፍልቅልቄ ዶቃ ያልበሰልኩኝ ጮርቃ
ያኔ ህፃን ሆኜ ከጡቱ ሰበቃ
አቦጊዳ ፊደል የቀለም ቀፈፋ
ብዕር ወረቀቱ አንጎሌን ሲያፋፋ
ሳቅሽ መቸ ገባኝ ቀልብ እንደ'ሚያጠፋ ።
ማር ይሳቅ መንገዱ የብርሃን ማማ
ቁራንም ሲቀራ ሲሰማ መንዙማ
ውዳሴ ማርያሙ ዜማና ቀሰማ
ምንድነው ነገሩ ውዴ ስሚኝማ
ፍቅርሽ እልል ብሎ ከኔ ማይሰማ ።
ምንድነው የሚሉት የልብን ስጦታ
ባላወኩት ጥበብ መንገዴ ተከፍታ
በናፍቆትሽ ገመድ ስታሰር ስፈታ
ሳቃ'ስት ውላለው ባልገባኝ እንድምታ ።
እንቺን እያሰበ ሰውነቴ ቀልጧል
ሌሊቱ ተጋምሶ ቀኔ ተሰዉቷል
ዓይኔ እያለቀሰ ተደስቶ ሟሙታል
በእንባዎች ዘለላ ከረጢቱ ደርቋል
ተንዶ ከቦታው ተበዝብዞ ጠፍቷል።
አስተዋይ አይደለሽ ፍቅር አድምጭማ
መውደድ ብርሃን ነው ያሳያል ጨለማ
አይኔን ውሰጅልኝ አልፈልግም ማያ
ልቤን መልሽልኝ ለነፍሴ ማቆያ ።
ተፃፈ በዘመን (B*)
ማስታወሻ ለ. . . .
የስንኝ ቋጠሮ ግጥም እየላቀ
ሁሉንም ባንድነት ሚዛን የጠበቀ
ሀገር ፡ፍቅር ፡ስሜት ባንድ እየረቀቀ
በበውቀቱ ስዩም ተጋምዶ ደመቀ!
ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@wengalmark
144 views19:17