Get Mystery Box with random crypto!

#UNHRC የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መርማሪ ኮሚሽን የሥራ ጊዜ ለአንድ ዓመት | 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹

#UNHRC

የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መርማሪ ኮሚሽን የሥራ ጊዜ ለአንድ ዓመት ተራዝሟል ፤ የስራ ጊዜው የተራዘመው ትላንት አጄኔቫ ውስጥ የተመድ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ም/ቤት አባላት ውሳኔውን በተመለከተ በሰጡት ድምጽ ነው።

የውሳኔ ሀሳቡ ጠባብ በሆነ የድምፅ ልዩነት ነው ተቀባይነት ያገኘው።

47 አባላት ካሉት የምክር ቤቱ አባላት መካከል የመርማሪ ቡድኑን ሥራ መቀጠል 21 ሀገራት ሲደግፉት 19ኙ ተቃውመውታል።

ከማላዊ " ድምፀ ተአቅቦ  " በስተቀር የምክር ቤቱ አባል የሆኑ ሁሉም የአፍሪካ አገራት ውሳኔውን ተቃውመውታል።

የደገፉ ፦

- አርጀንቲና
- አርሜኒያ
- ብራዚል
- ቼክ ሪፐብሊክ
- ፊንላንድ
- ፈረንሳይ
- ጀርመን
- ሁንድራስ
- ጃፓን
- ሉቱንያ
- ሉክዘንበርግ
- ማርሻል አይላንድስ
- ሜክሲኮ
- ሞንቴኔግሮ
- ኔዘርላንድስ
- ፓራጓይ
- ፖላንድ
- ኮርያ ሪፐብሊክ
- ዩክሬን
- ዩናይትድ ኪንግደም
- አሜሪካ

የተቃወሙ ፦

- ቤኒን
- ቦሊቪያ
- ካሜሮን
- ቻይና
- ኮትዲቯር
- ኩባ
- ኤርትራ
- ጋቦን
- ጋምቢያ
- ህንድ
- ሊቢያ
- ሞሪታንያ
- ናሚቢያ
- ፓኪስታን
- ሴኔጋል
- ሶማሊያ
- ሱዳን
- ዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ
- ቬንዙዌላ

ድምፀ ተአቅቦ ፦

- ኢንዶኔዥያ
- ካዛኪስታን
- ማላዊ
- ማሌዥያ
- ኔፓል
- ኳታር
- ሁዝቤክስታን

የውሳኔ ሀሳቡን መፅደቅ ተከትሎ በተ.መ.ድ. የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ፅ/ቤት (ጄኔቫ) ባወጣው መግለጫ ፤ የውሳኔ ሀሳቡን የተቃወሙ እና አጋርነትን ላሳዩ ፣ የድምፀ ተአቅቦ ላደረጉ የም/ቤት አባላት ምስጋና አቅርቦ ፤ በሰጡት ድምፅ ጣልቃ ገብነትን፣ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ማተራመስንና ማደፍረስን ነው የተቃወሙት ብሏል።

ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
@wektawi_Merej