Get Mystery Box with random crypto!

«ጉድ ሆንኩኝ ዛሬ...!» ይላል ጭንቅላቱን በሁለት እጆቹ ጭብጥ... ልቅቅ... ውርጭት እያደረገ. | ወግ ብቻ

«ጉድ ሆንኩኝ ዛሬ...!» ይላል ጭንቅላቱን በሁለት እጆቹ ጭብጥ... ልቅቅ... ውርጭት እያደረገ... የእልህና የሀዘን ዲቃላ እንባውን ..ከዐይኑ እየጠረገ... አስፓልቱ ያቆራቸውን የውሀ ኩሬዎች በቆዳ ጫማው ጠርዝ በእልህ እየረጫጨ... በላዩ ላይ የሚወርደውን ካፊያ ከምንም ሳይቆጥር በቀስታ ይጓዛል። መሀል ላይ «ወይኔ ተዋረድኩ ዛሬ!» ይላል።

በዚህ ወር ብቻ ሰባተኛ ሥራ ከእጁ ወጥቷል። ከዚያ በፊት በነበሩት ስድስት ወራት የቀድሞ ደንበኞቹ በተለያየ ምክንያት ትተውት... አዳዲስ ደንበኞች ማጥመድ ተስኖት... ሥራ በጨረታም... በልመናም... በልምምጥም እየሞከረ አልተሳካለትም። መጨረሻ የተገኘችው ስራ ሁለት ወይ ሶስት ወር ያልፋታል... የዛሬዋ ግን ከሁሉም አንገብግባዋለች። ተስፋውን ሁሉ ጥሎባት ነበርና ማጣቱ ወፈፍ ሊያደርገው ደረሰ። «ወይኔ ተዋረድኩ... በተከበርኩበት ሀገር!» ይላል እየተንተባተበ።

አስራ ሶስት ሰራተኞች ቀጥሮ ያሰራል። የሰራተኞች ደሞዝ፡ የቢሮ ኪራይ አለበት። የመጋዘን ኪራይ... የመኪና ኪራይ የጥሬ እቃ... የመብራት ፡ የውሃ ...የስልክ... የኢንተርኔት... የነዳጅ....የግብር የፍቃድ ማደሻ... ስም ያለው ስም የሌለው መዓት ወጪ አለበት። በዚያ ላይ ስራ ባጣባቸው ወራት ወጪዎቹን ለማስታገስ ብሎ ከስንት ተቋም...ከስንት ሰው ብር ተበድሯል። በዚያ ላይ የሱ ኑሮ ደሞ አለ። የመኖሪያ ቤት ኪራይ...ልጆቹ ትምህርት ቤት... የቤት አስቤዛ ወጪ... የእናቱ ሕክምና እና ሌላ የወጪ ክምር ደግሞ በገዛ ኑሮው በኩል ይጠብቀዋል።

እሱ ግን መንቀሳቀሻ ሳንቲም እንኳ ከኪሱ ከጠፋ ከራርሟል... ኮትና ሱሪውን ለብሶ ለትራንስፖርትና ለምሳ መክፈል እያቃተው ባዶ ሆዱን በእግሩ ስንት ቦታ እንደተንከራተተ የሚያውቀው የሰማዩ ጌታ ብቻ ነው። ግን ከሁሉም የዛሬዋ ቁስሉ ባሰች። ተስፋውን ሁሉ አሟጥጦ አሸክሟት ነበርና... ስትወድቅ አብሮ ሁሉ ነገሩ ወደቀበት... ተስፋ ቆረጠ።

የገዛ መስሪያቤቱ የሰራተኞቹን ዐይን ላለማየት ብሎ ከሄደ ሰነባብቷል። ስልክ ማንሳት እንደጦር ይፈራል። መንገድ ላይ ከአበዳሪዎቹ አንዱ እንዳያዩት ኮፍያና መነፅር ማድረግና ውስጥ ለውስጥ መንገድ ማቋረጥ ልማዱ ሆኗል። ዛሬ ግን እየተንተባተበ... ዝናብ እያረጠበው በተከበረበት በዋናው ጎዳና ላይ... ያለኮፍያና መነፅር ጭንብል... እንደእብድ ጮክ ብሎ እያወራ እንደልጅነቱ ውሃ እያንቦራጨቀ... ወደገዛ መስሪያ ቤቱ ደመነፍሱን እየሄደ ነው።

ሰዓቱ ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት ጥቂት አልፏል። የሰራተኞች መውጫ ሰዓት ማለፉን እንኳ ሳያገናዝብ እየተወራጨ መስሪያ ቤቱ ደረሰ። ምን ሊያደርግ እንዳሰበ አላወቀም። ግን ምንም ብርሃን አይታየውም። ጨለማ ነው። ከዚህ አይነት ውርደት ሞት የተሻለ እንደሆነ አንዳች መንፈስ ሹክ ይለዋል። የእልህ እንባ እና ሳግ እያደናቀፈው አሁንም አሁንም... «ኧረ መቅለል...! » እያለ የመስሪያቤቱን ደረጃ በፍጥነት ወጥቶ መግቢያው መጋዝን ጋ ሲደርስ ቆመ።

ለቢሮነት የተከራያቸው ክፍሎችና የስፌቱ መጋዝን በሕንፃው አንደኛ ፎቅ ላይ የሚገኙ ናቸው። ሕንፃው ላይ የሚሰሩት ሁሉም ሰራተኞች ባለመኖራቸው ከውጭ ምንም የሰው እንቅስቃሴ አይታይም። የሱ ቢሮዎችና መጋዘኑ ያለበት አንደኛው ፎቅ ግን በብርሃን ደምቆ ነበርና ገና እንዳየው ተናደደ። «እኔ ለራሴ የእዳ ማእበል ሊወስደኝ አሰፍስፏል...ጭራሽ መብራት አብርተው እየሄዱ ውዝፍ እዳ ሊከምሩብኝ ነው? a bunch of stupid people» ብሎ ሰራተኞቹን ተራግሞ ሰዓቱን ጎንበስ ብሎ አየ... ለአንድ ሰዓት አስር ጉዳይ። « ወይኔ የማንም መሀይም መቀለጃ ሆንኩ!» ብሎ መጋዝኑን ለመክፈት ቁልፍ ከኪሱ አውጥቶ ሊያስገባ ሲል የመጋዝኑ በር አልተዘጋም ነበርና... ወለል ብሎ ተከፈተ።

በንዴት ጦፎ ወደ ውስጥ ሲገባ ... ሁሉም ሰራተኞች በፍጥነትና በትጋት ስራቸውን እየሰሩ አየና በድንጋጤ ፀጥ አለ። መምጣቱን ስላላዩ ወደርሱ አልዞሩም ያለአንዳች መናጠብና ግዜ ማባከን በጥራትና በብቃት ስራቸውን እየሰሩ ነው። ቀስ ብሎ አንገቱን እያሽከረከረ ሁሉንም ሰራተኞቹን ቃኘ... የሚያወራ እና ስራ የፈታ አንድም የለም። ቀስ ብሎ የኋሊት ተራምዶ ወደሌሎቹም ቢሮዎች ሄደ። ሁሉም ሰራተኞች በትጋት እየሰሩ ነው። የቀረ .... ያልመጣ ... የእረፍት ጊዜዬ ደርሷል ብሎ አቋርጦ የወጣ የለም። ሁሉም አለቃቸው ሳይሰልላቸውና ሳይቆጣጠራቸው... እስከዚህ ሰዓት አምሽተው ሊያውም በእረፍት ቀን እየሰሩ ነው።

ቀሰስ ብሎ ወደገዛ ቢሮው ሄደና ወንበሩ ላይ ተቀመጠ። ተስፋ የመቁረጡ ስሜት ለራሱ አናደደው። «እንዴት ያለእረፍት ... ሳልቆጣጠራቸው... ሀያአራት ሰዓት... ሰባት ቀናት... ወሩን አመቱን ሙሉ የሚለፉልኝ የሚተጉልኝ ባለሞያ ሰራተኞች ይዤ ተስፋ እቆርጣለሁ? ተሳካለት? ወይስ አልተሳካለት ሳይሉ... ቢሮ ገባ አልገባም ሳይሉ... ደሞዝ ዘገየብን ቆየብን ሳይሉ... ሰራተኞቼ እየለፉ እኔ ምን ነክቶኝ... ምን ገጥሞኝ.. ምን ከብዶኝ... ተስፋ እቆርጣለሁ? አለ። ብቸኛው... ስራ ፈት እኔ ነኝ። እንጂ በስሬ የማይሰራ የለም። ብቸኛው ሰነፍ እኔ ነኝ ... እንጂ በስሬ ያልበረታ የለም አለ... አለና ልብሱን አስተካክሎ በግለት እየሮጠ ወጣ ...

እሱ ሲወጣ አንተ የት ጋ ነህ ወንድሜ?
ሰራተኞችህን እያቸው እስኪ አይንህን ጨፍንና። ልብህን እያት አንተን ጌታዋን ታምና ...ብታያትም ባታያትም ከማሕፀን ከመመስረትህ ጀምሮ ያለማቋረጥ እየተንደቀደቀች እየሰራች ነው። ኩላሊትህ ፈሳሽ ከማጣራት አልቦዘነም። ሳንባዎችህ ንፁህ አየር ከማስገባት የተበከለውን ከማስወጣት ተዘናግተው አያውቁም። ጉበትህ አንጀትህ ጨጓራህ... እግሮችህ... እጆችህ... ጆሮዎችህ አይኖችህ ምላስና ከንፈርህ... የደም ስሮችህ ...የነርቭ ጅማቶችህ... እጢዎችህ... የምታውቃቸውም የማታውቃቸውም እልፍ ሰራተኞችህ አንተ እንደአንተ እንድትቆም እንድትራመድ እንድታስብ እንድትኖር... የእድሜ ዘመንህን ያክል ያለእረፍት እየተጉ እየለፉ ነው። አለቃቸውን አንተን ሕያው ለማድረግ ስትቆጣጠራቸውም ሳትቆጣጠራቸውም የሞያቸውን ያክል የባህሪያቸውን ያክል ይለፋሉ። እንዴት ብትጨክንባቸው? እንዴት ብትንቃቸው? እንዴት ብታቃልላቸው? እንዴት ከመጤፍ ባትቆጥራቸው ነው ተስፋ የቆረጥከው ወንድሜ?

ምን ችግር ምን መከራ ቢገጥምህ... ምን ብትዝል ምን ብትንገሸገሽ... ቅን ሰራተኞችህስ? ልፋታቸውስ? እነሱ ቆመው እያደሩ ወድቀህ ልትቀር? እነሱ እየተራወጡ እየዋሉ አንተ ፈዝዘህ ልትመክን? ትጉህ ሰራተኞች የነበሩት ወዳቂ... ባለሞያዎች የሚለፉለት ብኩን ልትሆን? ይሄን ሁሉ በብርሃን በጨለማ ቢታሰስ ቢፈለግ የማይገኝ የኤክስፐርት መዓት ሰብስበህ መስሪያቤቱን ልትዘጋው? ልትተወው? ልትዘነጋው? ልትጥለው? ተስፋ ልትቆርጥ?

እህቴ...እንዴት ያለእረፍት ... ሳትቆጣጠሪያቸው... ሀያአራት ሰዓት... ሰባት ቀናት... ወሩን አመቱን ሙሉ የሚለፉልሽን የሚተጉልሽን ባለሞያ ሰራተኞችሽን ይዘሽ ተስፋ ትቆርጫለሽ? ተሳካላት? ወይስ አልተሳካላት ሳይሉ... ተኛች አልተኛችም ሳይሉ... ምግብ ...ዘገየብን መድሃኒት ቆየብን ሳይሉ... ወደውስጥሽ የምትዶያቸው የመርዝና የኬሚካል መአት ሳይበግራቸው... ሰራተኞችሽ...እየለፉ አንቺ ምን ነክቶሽ... ምን ገጥሞሽ.. ምን ከብዶሽ.. ለውጫዊ ሰው... ለውጫዊ ነገር... ለውጫዊ ሁኔታ ብለሽ...ተስፋ ትቆርጫለሽ? ። ብቸኛው...