Get Mystery Box with random crypto!

WALTA_TV_ETH 🔉

የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth1 — WALTA_TV_ETH 🔉 W
የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth1 — WALTA_TV_ETH 🔉
የሰርጥ አድራሻ: @waltatveth1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 30.95K
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2022-10-04 10:37:00
ጠ/ሚ ዐቢይ የሳይንስ ሙዚየምን መረቁ

መስከረም 24/2015 (ዋልታ) በመኃል አዲስ አበባ በቀለበት ቅርጽ እና በጉልላት መልክ በድንቅ የሥነ-ህንጻ ጥበብ የታነፀው ሳይንስ ሙዚየም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተመርቋል።

በአይነቱ አዲስና ልዩ የሆነው የሳይንስ ሙዚየም አለም የደረሰበትን የቴክኖሎጂ ልህቀት የሚመጥን ሆኖ የተገነባ ሲሆን ለኢትዮጵያም የቴክኖሎጂ እድገት ትልቅ መሰረት የሚጥል ሙዚየም እንደሆነም ታምኖበታል።

ምረቃውን ተከትሎ ትኩረቱን በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ላይ ያደረገ የፓን አፍሪካ ኮንፈረንስ በማካሄድ ሙዚየሙ ስራውን በይፋ ይጀምራል።

ኮንፈረንሱ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዙሪያ ውይይት በማድረግ፣ የምርምር አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ እና ዘመናዊ መፍትሄዎችን ለማስቀመጥ የሚረዳ ይሆናል።

ሙዚየሙ በተጓዳኝም ኢትዮጵያ በአስገራሚ ፍጥነት በማደግ ላይ ካለው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ጋር ለመጣመር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እንደሆነ ተመላክቷል።

ሙዚየሙ በ7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን በኪነ-ህንጻ ንድፍ ውስጥ ያካተተው ክብ ቅርጽም በማያቋርጥ እድገት ውስጥ ያለን እድገትና የሰው ልጆችን ጥበብ የሚያመለክት ነው ተብሏል።

ትልቁ ህንጻ ከ15ሺህ ሜትር ካሬ በሚበልጥ መሬት ላይ ያረፍ ሲሆን አጠቃላይ ስፋቱ 132 ሜትር ያህል ነው ተብሏል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
205 views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 21:07:37
የኢትዮጵያና ህንድ አጋርነት በተለያዩ ዘርፎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ

መስከረም 23/2015 (ዋልታ) የኢትዮጵያና ህንድ አጋርነት በኢንቨስትመንት፣ ንግድ፣ ቴክኖሎጂና ትምህርት ዘርፎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምሥራቅ፣ ኤስያ እና ፓስፊክ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጄነራል አምባሳደር ገበየሁ ጋንጋ ከህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል አምባሳደር ቡኒት ኩንዳል ጋር ተወያይተዋል።

አምባሳደር ገበየሁ ጋንጋ የህንድ እና የኢትዮጵያ ታሪካዊ ዘመናትን ያስቆጠረው ግንኙነት በኢኮኖሚና በባህላዊ መስኮች የቆየ ወዳጅነት እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

ይህ የሁለትዮሽ ግንኙነት ዛሬ ላይ ዘርፈ ብዙ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገልጸዋል።

በቅርቡ የኢትዮጵያ እና የህንድ የምክክር ፎረም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ጠቁመው በህዝብ ለህዝብ ግንኘነት፣ በባለብዙ ወገን ግንኘነት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይም በትብብር እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

አምባሳደር ቡኒት ኩንዳል በበኩላቸው የሁለትዮሽ  ግንኙነቱን ይበልጥ ለማሳደግ በኢንቨስትመንት፣ በንግድና በቴክኖሎጂ እንዲሁም በትምህርት ዘርፎች ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ እንደመሆኗ እና በምስራቅ አፍሪካ ያላትን ተፅዕኖ ፈጣሪነት በመጠቀም በእድገት እና በልማት የትብብር ዘርፎች በጋራ እንሰራለን ማለታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
1.2K views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 21:07:37
ከተማ አስተዳደሩ በዓላት በስኬት እንዲጠናቀቁ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ሰጠ

መስከረም 23/2015 (ዋልታ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሰሞኑ የተካሄዱትን ህዝባዊ በዓላት ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን በተላበሰ መልኩ እንዲከበሩ ከፍተኛ ሚና ላበረከቱት የፀጥታ አካላት፣ የሃይማኖት ተቋማትና አባ ገዳዎች እውቅና እና ምስጋና ሰጠ፡፡

በእውቅናና ምስጋና መርኃ ግብሩ የተገኙት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም ወዳድነት የአደባባይ ህዝባዊ በዓላት በአስቸጋሪ ወቅት ላይ ሆነን ከምንም ጊዜ በላይ ውጤታማ በሆነ መልኩ ማክበር መቻሉን ገልፀዋል።

ህዝባዊ በዓላቱ ያለ ምንም ልዩነት የጋራ በዓሎቻችን ናቸው በማለት ሁሉም በያለበት የበኩሉን አስተዋጽኦ በማድረግ የኢትዮጵያን ገፅታ ከፍ ባለ መልኩ ማክበር ችለናልም ነው ያሉት።

ከንቲባዋ ተቀራርበንና ተደጋግፈን በመስራትና በመተባበር በሌሎች ሥራዎቻችን ላይ ውጤታማ መሆን እንደምንችል የታየባቸው ህዝባዊ በዓላት እንደነበሩም አንስተዋል።

አሁን ላይ ህዝባዊ በዓላትን በአደባባይ ወጥቶ ለማክበር ምቹ ባልሆነበት ሁኔታ በሰላም ወዳዱ ኢትዮጵያውያን፣  በፀጥታ አካላት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባገዳዎች፣  በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ቅንጅት በዓላቱ ስኬታማ ሆነው መጠናቀቃቸውን ጠቁመዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች በሁሉም ደረጃ ህዝባዊ በዓላቱ እጅግ ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቁ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና ማቅረባቸውን ከከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
967 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 21:07:36
ም/ርዕሰ መስተዳድሩ የደንማርክ አምባሳደርን አነጋገሩ

መስከረም 23/2015 (ዋልታ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ካትሪን ስሚዝን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ የዴንማርክ መንግሥት በክልሉ ደን ሀብት አጠባበቅ እና የማኅበረሰብ የኑሮ ማሻሻያ ላይ እያደረገ ስላለው ድጋፍ አመስግነዋል፡፡

በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የደን ሀብቶችን የማስፋትና ስነ ምህዳርን የመጠበቅ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ለአምባሳደሯ አስረድተዋል፡፡

አምባሳደር  ካትሪን ስሚዝ ክልሉን በመጎብኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸው በዘርፉ የሚደረገው ድጋፍ  ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ማረጋገጣቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡

በዴንማርክ መንግሥት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ደንን መሰረት ያደረገ የኑሮ ማሻሻያ ድጋፍ ላይ እየተሠሩ ያሉ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራሞችን ጎብኝተዋል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
830 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 21:07:36
በሴካፋ ውድድር ሶማሊያ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ኢትዮጵያን አሸነፈች

መስከረም 23/2015 (ዋልታ) የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበራት ምክር ቤት (ሴካፋ) ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ውድድር ሶማሊያ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ኢትዮጵያን አሸነፈች፡፡

በመጀመሪያ አጋማሽ ሶማሊያ ባስቆጠረችው አንድ ጎል ጨዋታው ተጠናቋል፡፡
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
813 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 21:07:36
አትሌቱ ከማንኛውም ውድድር ለ5 ዓመት ከ4 ወር ታገደ

መስከረም 23/2015 (ዋልታ) አትሌት ታዬ ግርማ የተከለከለ የስፖርት አበረታች ቅመም በመጠቀሙ ለ5 ዓመት ከ4 ወር ከማንኛውም የስፖርት ውድድር መታገዱን የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን አስታወቀ።

ከመጋቢት 28 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ አትሌቱ ያስመዘገባቸው ውጤቶች እንዲሰረዙና በውድድሮቹ ያገኛቸው ሽልማቶች ተመላሽ እንዲሆኑ ውሳኔ ማስተላለፉን ባለስልጣኑ አመላክቷል።

መጋቢት 28 ቀን 2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው 50ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ እንዲሁም ሰኔ 13 ቀን 2013 ዓ.ም በጣሊያን ቴሌሴ ቴርሜ ከተማ በተከናወነው የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ላይ በተደረገው የአበረታች ቅመሞች ምርመራ አትሌት ታዬ ግርማ ‘Erythropoietin’ የተሰኘ የተከለከለ አበረታች ቅመም ሁለት ጊዜ መጠቀሙን የሚያመላክት ውጤት ማግኘት መቻሉን አመላክቷል።

ባለስልጣኑ ውጤቱን ተመርኩዞ በአትሌት ታዬ ላይ ጊዜያዊ እገዳ በመጣል ባካሄደው ምርምራ አትሌቱ ጥፋተኛ ሆኖ አግኝቶታል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡

በተጨማሪም አትሌት ታዬ ከመጋቢት 28 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ያስመዘገባቸው ውጤቶች እንዲሰረዙ እና በውድድሮቹ ያገኛቸው ሽልማቶች ተመላሽ እንዲሆኑ የቅጣት ውሳኔ እንደተላለፈበት ነው ባለስልጣኑ የጠቆመው።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
803 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 21:07:36
ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋምቤላ ገቡ

መስከረም 23/2015 (ዋልታ) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ተስፋዬ በልጅጌና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋምቤላ ከተማ ገቡ።

የስራ ኃላፊዎቹ ጋምቤላ ከተማ የተገኙት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በሚያዘጋጀው 11ኛው "ስለ ኢትዮጵያ" የፎቶግራፍ አውደ ርዕይና የፓናል ውይይት ለመሳተፍ ነው።

የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋምቤላ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የጋማቤላ ክልል ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ከፎቶ ግራፍ አውደ ርዕዩ ጎን ለጎንም "ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች " በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት እንደሚካሄድ ይጠበቃል።
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
937 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 14:22:13
በአደባባይ በዓላት ላይ ሁከት ለመቀስቀስ ሲያሴሩ የነበሩ 166 የሽብር ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ

መስከረም 23/2015 (ዋልታ) በመስቀል የደመራ ሥነስርዓት እንዲሁም በአዲስ አበባ እና በቢሾፍቱ በተከበረው የኢሬቻ በዓል ላይ የሽብር ተግባር በመፈጸም ሀገራዊ ቀውስ እንዲፈጠር በህቡዕ ሲያሴሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡

የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ አሸባሪ ቡድኖች በመስከረም ወር በሚከበሩት የአደባባይ በዓላት ላይ ሁከትና ብጥብጥ በመቀስቀስ ሀገራዊይዘት ወዳለው ቀውስ እንዲሸጋገር በህቡዕ ሴራ ሲጠነስሱ ነበር፡፡ ይሁንና የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል የአደባባይ በዓላቱ ሰላማዊ ሆነው እንዲጠናቀቁ ባደረገው ጠንካራ ቅድመ ዝግጅትና ምስጢራዊ ክትትል ሴራውን ከውጥኑ ማክሸፍ ተችሏል፡፡

በዚህም 166 የህወሓት፣ የሸኔ፣ የአይ ኤስ እንዲሁም የኢመደበኛ አደረጃጀት አባለት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል፡፡

የአሸባሪ ቡድኑ አባላት በመስቀል የደመራ ሥነስርዓት እንዲሁም የኢሬቻ በዓል በሚከበርባቸው አዲስ አበባ እና ቢሾፍቱ ሁከትና ብጥብጥ የመቀስቀስ ተልዕኮ ተቀብለው በህቡዕ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር የጠቆመው የጋራ ግብረ ኃይሉ መግለጫ፤ በተለይ አሸባሪው ሸኔ የሽብር ተግባር የሚፈጽሙ ሴሎችን ሲያደራጅ እና አባ ቶርቤ የተባለውን ገዳይ ቡድን ለማሰማራት ሙከራ ሲያደርግ መቆየቱን ጠቅሷል፡፡

ለዚሁ የጥፋት ተልዕኮውም ከህወሓት የሽብር ቡድን ጋር በመቀናጀትና የሎጀስቲክስ አቅርቦት በማመቻቸት ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን አመልክቷል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
882 views11:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 14:22:13
የሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ውድድር መካሄድ ጀመረ

መስከረም 23/2015 (ዋልታ) የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበራት ምክር ቤት (ሴካፋ) ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ውድድር መካሄድ ጀመረ፡፡

ሙሉ ጨዋታው በዋልታ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ኮርፖሬት በሁሉም የሚዲያ አማራጮች በቀጥታ እየተሰራጨ በመሆኑ እንድትከታተሉን በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
694 views11:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 14:22:13
መንግስት በዓላት በሠላማዊ ሁኔታ መጠናቀቃቸው የህዝቡን የሠላም ዘብነት ያሳየ ነው አለ

መስከረም 23/2015 (ዋልታ) ህዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላት በፍፁም ሠላማዊ ሁኔታ መጠናቀቃቸው የህዝቡን ጠንካራ የሠላም ዘብነት ያሳየ መሆኑን የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡

በመስከረም ወር ኢትዮጵያ አምራ የታየችባቸው ህዝባዊ እና ኃይማኖታዊ በዓላት በድምቀትና በሰከነ ሁኔታተከብረዋል፡፡

የአዲስ አመት አቀባበል ከዋዜማዉ ጀምሮ፤ የመስቀል በዓል፤ ኢሬቻ እና የግሸን ደብረ ከርቤ በዓላት፣ በደቡባዊ ኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎችና ዞኖች የተከበሩ በዓላትም ጭምር ያለምንም የፀጥታ ችግር በሚሊዮኖች በሚቆጠር ህዝብና በርካታ ቱሪስቶች ተሳትፈውባቸው ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ይዘታቸውን ጠብቀውና በታላላቅ ፈጠራ ታጅበው በድምቀት ተከብረዋል፡፡

https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0UvW4xxSRf5doMQUjFAxiWoGuuswAcAY5iFxzHipNPKeKQrBwViq3DGmPoGgkejTsl

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
636 views11:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ