2022-10-11 20:24:29
የሀገራችንን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ወጣቶች የአምባሳደርነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ
ጥቅምት 1/2015 (ዋልታ) ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ወጣቶች የአምባሳደርነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ተናገሩ።
ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ወንድማማችነትን የመትከል አረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብርን በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ከቀናት በኋላ ታካሂዳለች።
በተለያዩ የጎረቤት ሀገራት ለአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርኃ ግብር ለሚሄዱ ወጣቶች ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በተገኙበት ሽኝት ተደርጎላቸዋል።
ለወጣቶቹ መልዕክት ያስተላለፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በተለያዩ የዓለማችን ክስተቶች ቀዳሚ እንደነበረች አስታውሰዋል።
በተለይ በተለያዩ ሀገራት በሰላም ማስከበር ዘርፍ ጠንካራ ስራዎች ማከናወኗን ገለጸው የአረንጓዴ አሻራ የወንድማማችነት መርኃ ግብርም የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ አንዱ አካል መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ጥንካሬዋና እድገቷ የሚወሰነው በወጣቶች በመሆኑ ሁሉም የራሱን ኃላፊነት በሚገባ በመወጣት አሻራውን ማስቀመጥ እንዳለበት አሳስበዋል ሲል የዘገበው ኢብኮ ነው።
"ፕላንት አፍሪካን ፍራተርኒቲ" ዝግጅት ኢትዮጵያ የጀመረችውንና በስኬት እያከናወናችው ያለውን የአረንጓዴ አሻራ ወደ ጎረቤት ሀገራትም ማስፋፋት አላማውን ያደረገ መርኃ ግብር ነው።
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth1
አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
705 views17:24