ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የጣሊያን፣ የጅቡቲ፣ የሶማሊያ እና የኬንያ የመሪዎች ስብሰባን ተሳተፉ ሐምሌ 17/2015(ዋልታ)ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ኢትዮጵያን ጨምሮ የጣሊያን፣ የጅቡቲ፣ የሶማሊያ እና የኬንያ የመሪዎች ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል። ስብሰባው በሀገራቱ መካከል የተቀናጀ ትብብር እንዲኖር የጋራ በሆኑ ጉዳዮች እና ፍላጎቶች ላይ ለመማከር የተዘጋጀ መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል። 2.9K viewsedited 14:14