Get Mystery Box with random crypto!

የተፃፉ ሃሳቦች•°•°•°•

የቴሌግራም ቻናል አርማ tsihofoch — የተፃፉ ሃሳቦች•°•°•°•
የቴሌግራም ቻናል አርማ tsihofoch — የተፃፉ ሃሳቦች•°•°•°•
የሰርጥ አድራሻ: @tsihofoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 147
የሰርጥ መግለጫ

ልቦለድ /ኢ-ልቦለድ ብቻ በተከሸነ ጥኡም የብዕር ቀለማት
የሚለቀቅበት ቻናል ነው! …ሃሳብ ፣ የተፃፉ ፅሁፎች ካሎት @tizta4 ይጠቀሙ ………! @keneyalew_teweld
ንም ይጎብኙ !!!

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2020-06-04 07:15:24 ኑሮ

------- ዳዊት ፀጋዬ


ከደቦ 60 ደራስያን ከተሰባሰቡበት
መፅሀፍ የተወሰደ


"አትንካኝ!" ገላመጠችው።

"ለምን!?" እየተለሳለሰ ጠየቃት።

"ታስጠላኛለህ!"

"ቆይ ምን ሁን ነው የምትይኝ?" አቀርቅሮ ፀጉሩን
እያሻሸ።

"ደግሞ አንተ ምን መሆን ትችላለህ?" ጀርባዋን
ሰጠችው።

የተከራያት ጠባብ ክፍል፣ለጥቂት ደቂቃዎች
ፀጥታ የተከራያት መሰለ።

ከዚያ ከተቀመጠበት ተነስቶ ፣ "እሺ ይቅርታ አድር
ጊልኝ!" አለና እግሯ ላይ ወደቀ።

"እንጃልህ !" እግሯን ስታሸሽበት ወለሉ ተቀበለው

ከዚያው ባለበት ሆኖ እያለቃቀሰ ፣ "እሺ ምንድነ
ው ጥፋቴ!?" አላት።

"ልፍስፍስ! የወንድ አልጫ ማለት አንተ ነህ!"

"አዎ ነኝ" ቀና ብሎ በዕንባ በረጠቡ ዓይኖቹ እያያ
ት። እሷ ግን የበለጠ ንዴት አንቀጠቀጣት። መን
ቀጥቀጧን በሬክተር ካልሆነ መለካት ያስቸግራል

"እንዴት እግሬ ላይ ትወድቃለህ አንተ ሐሞተ ቢስ!
ደግሞ አዎ ነኝ እያለ ያረጋግጥልኛል እንዴ?ወይኔ
ዕድሌ! ከምኑ ላይ ጣለኝ እባካችሁ!" ጭንቅላቷን
በሁለት እጆቿ ይዛ።

"አሁን ውጣልኝ! ዓይንህን ማየት አልፈልግም!"

"የት ልሂድ የኔ ፍቅር?"

"እንጃለህ! ገደል መግባት ትችላለህ!" አንባረቀች
በት። ከአጠገቧ ተነስቶ ራቅ ብሎ ካለው ወንበር
ላይ ሄዶ ተቀመጠ።

"የዛሬ ሣምንት የማገባው አንተን ነው ማለት ነው
?!" ወደ በሩ ተንደረደረች ፤ ተከተላት።

* * *
የሠርጉ ዕለት እየፈራ ነበር ፣ እጁን ከእጆ ጋር
ያቆላለፈው። የሚራመደው የእርሷን ፊት እያየ
ስለነበር ፣ አንድ ጊዜ አደናቅፎት ሊወድቅ ሲል
እድምተኛው ሁሉ ሳቀ። ላብ አሰመጠው።ከዚያ
በኃላ ሊያያት እንኳን አልደፈረም። ምሳ ላይ ሊያጎ
ርሳት እጁን ሲዘረጋ ፣"አስቀምጠው ፤ እኔ አንስቼ
እጎርሰዋለሁ!"አለችው። እጁ እየተንቀጠቀጠ ሰሃኗ
ላይ አስቀመጠላት።ሚዜዎቹ "ምነው ጉርሻክን
እንቢ አለች !?" ሲሉት ፣ "ኧይ! ጉርሻውን ስላበዛሁ
ት ነው!" ሲል መለሰላቸው።

ማታ ጫጉላ ቤት ሲገቡ በረዥሙ ተነፈሰ። ከዚያ
እያፏጨ ፊቱን ኮስተር እንዳደረገ ፣ ልብሶቹን ካወ
ላለቀ በኃላ ዘወር ብሎ እንኳን ሳያያት አልጋው ው
ስጥ ገብቶ ተኛ። ድንገተኛ ባሕርይ ስለሆነባት
"ምነው!?" አለች ብርድ ልብሱን ሲከናነብ።

"እኔን ነው!?" አላት እንደተከናነበ። ወደ አልጋው
ተጠግታ በእጇ ስትነካው ፣ "እንዳትነኪኝ!"
ጆሮዋን በመጠራጠር፣ "ምን አልከኝ!?"

"እንዳትነኪኝ!" ደገመላት።

"ለምን!?"

"ታስጠዪኛለሽ!" አንገቷን ደፋች።

"ቆይ ምን አደረግኩህ!?" ግራ ገብቷታል።

"ደግሞ አንቺ ምን ማድረግ ትችያለሽ!?"ገልበጥ
ብሎ ጀርባዋን ሰጣት።

ጫጉላ ቤቱን ለጥቂት ደቂቃዎች ፀጥታ ወረሰው።
"እሺ ይቅርታ አድርግልኝ!"አለችና አልጋው ላይ
ወጥታ ብርድ ልብሱን ልትገልጠው ስትሞክር ፣
"እንጃልሽ!?" ድንገት ከወገቡ በላይ ቀና ብሎ ፣
ክንብንቡን ገልጦ ምራቁን ተፋባት።

"ምን! እኔ ላይ?"

"አዎ! አንቺ ላይ!" ተመልሶ ተኛ።
ተንሰቅስቃ አለቀሰች።
"አንቺ እኮ ሰው ያልሆንሽ ሴት ነሽ!"
"አዎ! ነኝ።ኧረ ሰውም ሴትም አይደለሁም!"
ማልቀሷን ቀጥላለች።
"አሁን ውጪልኝ! አንቺን ማየት አልፈልግም!"
"የት ልሂድ የኔ ፍቅር?" ትለማመጠው ገባች።
"እንጃልሽ ገደል መግባት ትችያለሽ።"አንባረቀባት

ከአልጋው ወርዳ ወንበሩ ላይ ተቀመጠች።

* * *
በሳምንቱ እርሷ ከሥራ ውላ እንደገባች፣እርሱን
ገላምጣ ወደ መኝታ ክፍል ገብታ የቴዲ አፍሮን
ዘፈን ቂጡ ድረስ በመክፈት አብራ ትዘፍን ጀመር።
እሱም ገዝቶ የመጣውን ሥጋ ከከተፈው በኃላ
መጥበሻ ላይ አድርጎ የአስቴርን ዘፈን በፉጨት
እያዜመ ይጠብስ ጀመር። ከዚያ እርሱ እያፏጨ
ሲበላ እርሷም እየዘፈነች በላች።

ከዚያች ቀን በኃላ የሚለምንም ፣ የሚለመንም፣
የሚያዝንም ፣ የሚያሳዝንም ፣ አልቃሽም ፣ አስለ
ቃሽም የለም። አሁን በቃ 'ኑሮ' ጀምረዋል።

* * *


ውብ አሁን

╭══•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀: ══╮
@tsihofoch
@tsihofoch
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ ══╯
283 views04:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-03 16:35:54 ……………#የቀጠለ
እና……………

ቀስ በቀስ አፈቀርኳት። አክማታለሁ ብዬ እኔው ራሴ መታመም ጀመርኩ። በፕሮግራማችን መሰረት ከሰኞ እስከ አርብ ባለው ጊዜ አፈቅርሻለሁ እላታለሁ።
እሷ አታውቅም እኔ ግን ከልቤ መናገር ጀምሬያለሁ።

ድምጼ አወጣጡ እንደድሮው አይደለም። እንደድሮው ድራማ ብቻ አይደለም። ህይወት ያለው እውነታ ነው። የሆነ ቀን
ላሳውቃት ፈለኩ እሁድ ቀን ነው፣ ከድራማ ነጻ የምንሆንበት ቀን…እና ደወልኩላት
<<እንዴት ነሽ>>
<<ደህና ነኝ>>
የምናገረው ጠፍቶብኝ ተደነባበርኩ
<<ምነው ጸጥ አልክሳ>> አለች
<<….ቤቲ…>>
<<አቤት!>>
<<እወድሻለሁ!!>>
<<እ?>>
<<እወድሻለሁ!>>
<<ዛሬ እሁድ መስሎኝ… ሰኞ ነው እንዴ?>> አለች በጥርጣሬ
<<ልክ ነሽ እሁድ ነው። ከምር ከልቤ …ከነፍሴ….አፈቅርሻለሁ!!>> እፎይ ብዬ ተነፈስኩ።
ከወዲያኛው የሲቃ ድምጽ ሰማሁ።
<<እየቀለድክብኝ እንዳይሆን…ምኔ…ምኔ ይወደዳል እኔ?>>
<<እብደትሽ! የዚያን ቀን ተሳስተሻል! እኔም ተሳስቻለሁ። ለመፈቀር ቆንጆ መሆን አይጠበቅብሽም>>
<<የምርህን ነው ?>> በሚቆራረጥ ድምጽ
<<አዎን>>
<<ወይኔ ጉዴ!>> ስታለቅስ በስልኩ ሾልኮ ይሰማኛል። የሆነ ጊዜ ላይ እንዳለቀሰችው አይነት ለቅሶ…ግን የሀዘን ሳይሆን የደስታ የሆነ!
<<በስልክ ያልከኝን…ባካል ልትለኝ ትችላለህ?>>
<<እንዴታ!>>
ስጣደፍ ወደቀጠረችኝ ቦታ አመራሁ። ምን አይነት ሁኔታ ውስጥ ልትሆን እንደምትችል ገመትኩ።

የመጀመርያ ፍቅሯ ነኝ። ለመጀመርያ ጊዜ አፈቅርሻለሁ ያልኳት እኔ ነኝ። ስንት
ዘመን ተሰዳ ያጣችው ፍቅር ራሱ እየመጣላት ነው። ስልክ ላይ ማልቀሷ ብዙም አልገረመኝም። ልክ ስደርስ በእንባ እየታጠበች ነበር ያገኘኋት። ሰላም ራሱ አላልኳትም። አይን አይኗን እያየሁ <<እወድሻለሁ!>> አልኳት። አይኖቿ አሁንም ባለማመን እንዳፈጠጡ
ናቸው። ፊቷ እንደረጠበ ነው። እጆቿ እየተንቀጠቀጡ ነው። <<ይህንን ለመስማት ምን ያህል እንደደከምኩ ታውቃለህ?>>
<<አውቃለሁ የኔ ፍቅር…>>
<<ይህ ቀን እንዲመጣ ምን ያህል ጊዜ እንደደከምኩ ታውቃለህ>>
<<አውቃለሁ የኔ ቆንጆ
<<….እድሜዬን በሙሉኮ ነው…>> ልታቅፈኝ እንኳ አልቻለችም። እየተንቀጠቀጠች ወደ
ሌላኛው ወንበር ሄደች። ከዚያ…አንድ የጃንቦ ትራፊ አንስታ ላዬ ላይ ገለበጠችብኝ።

<<አልፈልግህም ማለት አይገባህም!!! ያምሀል?? እብድ ከሆንክ ለምን ሆስፒታል አትሄድም በቃ ባንተ ምክንያት እንደፈለኩ መንቀሳቀስ አልችልም ማለት ነው?

>>….እየጮኸች። ግራ እየተጋባሁ ተዟዟርኩ። ሰው ከቦ እያየን ነው። እየተመናቀረችና እየተወራጨች..ትታኝ ሄደች።

በቃ ሔደች...just like that

ውብ አሁን

╭══•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀: ══╮
@tsihofoch
@tsihofoch
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ ══╯
263 viewsedited  13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-03 16:35:53 ስቅ! ስቅ! ስቅ! እምፍ! የሚል ቀጭን የሴት ለቅሶ ሰማሁ። የጆሮዬን መግላሊት እያዟዟርኩ ከወዴት እንደሆነ ለማወቅ ሞከርኩ።

ድምጹን እየተከተልኩ ስራመድ እንባዋን እንደነጠላ አጣፍታ ከለበሰች ሴት ጋር ተገጣጠምኩ ። ኩርምትምት ብላ ግድግዳው ስር ተወሽቃለች። ባንድ እጇ ምላጭ ይዛለች። ሌላኛው እጇ እየደማ ነው። ደም ስሯን ልትቆርጥ ስትል
እንደደረስኩባት ገባኝ። ደነገጥኩ። በፍጥነት ምላጩን ቀማኋት።

<<ምን ሁነሽ ነው?>> አፈጠጥኩባት
ዝም ብላኝ ለቅሶዋን ቀጠለች
<<….ምንድን ነው? በፈጣሪ!>>
<<….ተወኝ….አይገባህም…>>
<<ምንድን ነው እሱ?>>
<<አይገባህም አልኩህኮ>> አለችና አቀረቀረች።

በድንጋጤ አይኖቼን አፍጥጬ አያታለሁ።
ድንገት ቀጥ ብላ

<< እባክህ መጠጥ ግዛልኝ። መስከር እፈልጋለሁ!>> አለችኝ። ይህች ሴት <<ቤቴልሄም>> ናት። የምሰራበት መስሪያ ቤት ውስጥ በተላላኪነት ትሰራለች። በሚገርም ሁኔታ ከተቀጠርኩ
አንስቶ ሰላም ብያት እንኳ አላውቅም። ከስራ የመውጫ ሰአት ደርሶ ልወጣ ስል ነው እንዲህ ባንዱ ኮሪደር ስር ተሸርኩታ ያገኘኋት።

ቢሮ ውስጥ የነበሩትን ሁሉ ጠርቼ ተረባርበው ወደ ቤቷ ወሰዷት። ከዚያ በኋላ ለአንድ ወር አላየኋትም። ከስራ ቀረች። እኔ ደግሞ ወሩን ሙሉ ሳስባት ቆየሁ። ምን ነክቷት ይሆን እያልኩ።
ከወር በኋላ ስትመጣ ቢሮዬ አስጠራኋት።

<<ዛሬ እንዴት ነው መጠጣት ትፈልጊያለሽ>> አልኳት
<<አዎ>> አለችኝ።አንድ ሰአት እንድንገናኝ ቀጠርኳት። ስንገናኝ ከሰላምታ ውጭ ማውራት ከበደኝ። ራሱን ሊያጠፋ የነበረ ሰው ስለ ምን ሊወራ ይችላል። ዝም ተባባልን። ዝምታውን ተከትሎ ብዙ ቢራ ጠጣች! ጠጣች….ጠጣች…ጠጣች…..! ዝርክርክ አለች።

<<ምን ሁነሽ ነው ግን?>> አልኳት እንደምንም ተደፋፍሬ። ፊትለፊት የወደቀ ሎተሪ ነበር። ቢራ ተደፍቶበት በስብሷል። በጣቷ ወደሱ እየጠቆመች
<<….ልክ እንደዚህኮ ነው የተወኝ!>> አለችኝ
<<ማን ነው እሱ?>>
<<ቢንያም ነዋ! ሁለት አመት ሙሉ ፍቅሬን እንዲቀበለኝ ተንበርክኬ የለመንኩት ቢንያም!>>
<<እና ሁለት አመት ሙሉ እንቢ ካለሽ ምንድን ነው እንዳዲስ ያናደደሽ አልኳት>>
<<እንደምንም ቆጠረኝ። ካፌ ውስጥ ያ ሁሉ ሰው በተሰበሰበበት…ውሀ ደፋብኝ! < አልፈልግሽም ማለት አይገባሽም!!! ያምሻል?? እብድ ከሆንሽ ለምን ሆስፒታል አትሄጂም? በቃ ባንቺ ምክንያት እንደፈለኩ መንቀሳቀስ አልችልም ማለት ነው?> እያለ ጮኸብኝ። ያ ሁሉ
ሰው በተሰበሰበት አሸማቀቀኝ…አሁን አፈቅርሀለሁ መባል ውሀ ያስረጫል?>>
<<አያስረጭም!>> አልኩ። ከኛ ወንበር አለፍ ብሎ የተቀመጠው ሰው ስለምን እያወራን እንደሆነ ለማጣራት ጆሮውን ሲያቆም ይታየኛል።

<< ሴት ልጅ ክብሯን ትታ ወንድ ልጅን ለመነች ማለት ምን ማለት እንደሆነ ታውቃለህ?>>
<<አላውቅም!>> የቀረበልኝን ከአልኮል ነጻ መጠጥ እየተጎነጨሁ።
<<አዎ አታውቅም! አንተ ብቻ አይደለህም ብዙ ወንዶች አያውቁም>> በረጅሙ ተነፈሰችና በርበሬ የመሰለውን አይኗን አፈጠጠችብኝ
<<ለመሆኑ አንተ ለመልክህ ትጨነቃለህ? ጠዋት ስትነሳ ቆንጆ አይደለሁም የሚል ሀሳብ ይይዝሀል?>>
<<አይዘኝም>> መልኬን ያን ያህል ገምግሜው አላውቅም።
<<እኔ ግን እጨነቃለሁ። ቆንጆ አለመሆኔ ያስቆጨኛል። ገና ከት/ቤት ጀምሬ ወንድ ጠይቄ እንጂ ተጠይቄ አላውቅም። ለምን? ምክንያቱም ቆንጆ አይደለሁም። አንተ ወንድ ነህ። ለመኖር ጠንክሮ መስራት ብቻ ነው የሚጠበቅብህ። እኔ ግን በተፈጥሮ ቆንጆ መሆን አለብኝ። ቆንጆ ካልሆንኩ ሰዎች ብቃቴን አይተው ሊያደንቁኝ አይችሉም። ፊታቸውን ከእኔ
ያዞራሉ…ተፈላጊነት አይኖረኝም >>
የተናገረችውን ሳስበው ትክክል መሰለኝ። ሴት ልጅ የተዋበ ፊት ፣ ማራኪ ወገብ አልያም የሚያሻፍድ ዳሌ ከሌላት በብዙ መስክ ስኬታማነቷ ይቀንሳል። በሆነ ጉዳይ ላይ ብቃት ያላት ሴት በመልኳ የምትሳቀቅ ከሆነ ከሚዲያ መሸሿ አይቀሬ ነው። ጥሩ የትወና ብቃት እያላት
ቦዘኔ ልትሆን ትችላለች። ምርጥ ገጣሚ ሁና ሳለ ከመድረክ ልትሸሽ ትችላለች።
<<ለምን እንደሱ ትያለሽ? አሁን ብዙዎቹ አትሌቶች መልካቸው ከዚህ ግባ የሚባል ሁኖ,ነው? ስራቸው ነው ያስከበራቸው!>> አልኳት የግዴን።

<<…ልታጽናናኝ አትሞክር…ቁንጅና ለወንዶች ቅንጦት ለሴቶች ደግሞ እንጀራ ነው። እንጀራ ብቻ አይደለም ክንድ ነው። የሀይስኩል ተማሪ እያለሁ ጓደኞቼ የፍቅር ደብዳቤ እየደረሳቸው ሲዝናኑ እኔ ግን ሰላምታ እንኳን አይደርሰኝም። ታምነኛለህ? እስካሁን አንድ ሰው እንኳ
<እወድሻለሁ> ብሎኝ አያውቅም። ለምን ይለኛል? ደብዳቤ ቢጽፍልኝስ ምን
ይለኛል?..ፊትሽ ጨረቃ ነው ሊለኝ?..
ሃሃሃሃሃሃ>> ሳቋ የሚያስበረግግግ ነበር።
ከዚህች ሴት ጋር በንደዚህ አይነት ሁኔታ ማውራቴ ትንሽ አስፈራኝ።

የተንጨባረረ ጸጉርና የሚያሳቅቅ አለባበሷን ሳስተውል <አብዳ ይሆን እንዴ> ብዬ አሰብኩ…ብቻ ፈራኋት።
አስተናጋጁን ጠርቼ ሂሳብ ከፈልኩ።
ልነሳ ስል <<በናትህ…ልለምንህ…በሆነ ነገር እርዳኝ?>>አለችኝ እየተለማመጠች።
<<ምን ልርዳሽ>>
<< በቃ እኔም እንደሴቶቹ መለመን እፈልጋለሁ። ገብቶሀል ኣ? ወንድ ቀጥሮኝ መቅረት ፣ ሲደወልልኝ እየዘጋሁ ማንገላታት፣ የኔ ፍቅር እባክሽ ብሎ ሲንበረከክ ትቼው መራመድ….እንደሴቶቹ መሆን እፈልጋለሁ።በቃ ከቻልክ>>አለችና ጸጥ አለች <<ከቻልኩ ምን?>>
<<ከዚህ ስሜት እስክወጣ ደውልልኝ>>
<<ደውዬስ?>>
<<አፈቅርሻለሁ እያልክ ለምነኝ። ትንሽ ልንቀባረርብህ…ለተወሰነ ጊዜ ብቻ! እባክህ ለተወሰነ ጊዜ ለምነኝና የሴትነት ወጉ ይሰማኝ>>
እብደቷ ስለገረመኝ እሺ አልልኳት። እና ብዙ ብዙ ነገር አወራችኝ። ላይዋ ላይ የሰፈረው የዝቅተኝነት ስሜት ብዙ እንደጎዳት አስተዋልኩ። እንግዲህ ከሰኞ እስከ አርብ እየደወልኩ እንድለምናት ነው የጠየቀችኝ። ከሰኞ እስከ አርብ አፍቃሪዋ ሁኜ እተውናለሁ። እሷም ቆንጆ እና ኩራተኛ ሴት ሁና ትንቀባረርብኛለች …ከዚያ ቅዳሜና እሁድ ከትወናው ወጥተን በትክክል እናወራለን። እንደዛ እንዲሆን ነው የጠየቀችኝ። ሃሃ እብድ ናት!።
….
ሰኞ እለት ደወልኩላት። እየገረመኝም ሳቄ እየመጣኝም እንደምንም እያፈንኩ ነው ያወራኋት።
<<እባክሽ የኔ ቆንጆ አውሪኝ…>>
<<አትጨቅጭቀኝ አልኩህ አይደል እንዴ?>>
<<…በጣምኮ ነው የምወድሽ…>>
<<እኔ ደግሞ አልፈልግህም አልኩኮ>> ኮስተር ያለ ድምጽ!
….
ረቡእ!
<<የኔ ማር…በምትወጂው ሁሉ እለምንሻለሁ>>
<<ውይይይይይ! አሁንስ አንተ ልጅ በጣም እያማረርከኝ ነው>> (አልዋሽም እንዲህ ስትለኝ
ሳቄ ለጥቂት ሊያመልጠኝ ነበር)
….
ሀሙስ
<<ውዴ….አንቺኮ ማለት ለእኔ የልብ ትርታዬ ነሽ! ያላንቺኮ ምንም ነኝ>>
<<ለምት ትነዘንዘኛለህ? አንተ ደግሞ ለእኔ የልብ ድካሜ ነህ! ምን አይነቱ ነው?>> <በቃ
እብድ ነገር ናት> አልኩ በልቤ!!

እሁድ አንድ ካፌ ውስጥ ተቀምጠናል
<<ታውቂያለሽ ግን እብድ ነሽ!>> አልኳት
<<አንተ ደግሞ በጣም ቅን ሰው ነህ። ከልብ አመሰግናለሁ! ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ እያደረክ ነው። >> አለችኝ።
አንዳንድ ጊዜ ሳስበው ለማመን ይከብደኛል። ግን ሆነ። በዚህ ሁኔታ ከዚህች እብድ ልጅ ጋር ሁለት አመት ቀጠልን። በቃ እደውልላታለሁ። <<አፈቅርሻለሁ፣ እወድሻለሁ፣ ህይወቴ ነሽ>> ምናምን እላታለሁ (ራሷን ልታጠፋ የሞከረች ልጅ ማከሜ ነው በእኔ ቤት) እሷ ደግሞ አጸፋውን በኩራትና በቁጣ ተሞልታ ትመልሳለች። ቅዳሜ እና እሁድ ግን ራሳችንን ሁነን ስለሳምንቱ እያወራን እንዝናናለን። በዚህ ሁኔታ ተላመድን። መላመድ ክፉ ነገር ነው። እብደቷን ወደድኩት።
243 viewsedited  13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-02 09:39:46 ብቻዬን መሆን ፣ፀጥታ ፈልጌ በተቀመጥኩበት ድንገት ጎረቤት እየተክለፈፈፈች ትመጣለች

<ለምን ብቻሽን ተነሺ ከሰው ሲጫወቱ ነው ደግ > አራት ነጥብ የሌለው የወሬ ዶፍ ታወርድብኛለች "አይ ብቻዬን መሆን እፈልጋለው አልልም በይሉኝታ ታስሪያለው ።

ልቤ "እንቢኝ" እየያለ ፣ ልማደኛው አፌ እሺ ይላል። ማልወደው መዳፍ ሙሉ ጉርሻ እንቢ ላለማለት የግዴን አላምጣለው፣ <አንድ ያጣላል
በሞቴ ፣ይጣፍጥል > ሌላኛው ጉርሻ እቀበላለው።

በይሉኝታ ተሸብቤ ፣"በምን ይሉኛል "
#ታስሪያለው ። የማልወደው ተቀብዬ ፣ላለማደንቀው አጨብጭቤ ፣በማያስቀኝ ገለፍጣለው።

ለይመስል እየኖርኩኝ ፣ በይሉኝታ ድር ተተብትቤ የሚፈልጉትን ኖሬ ፣ሳልፈልግ ሞታለው።

አልፈልግም ፣አልወድም ፣አይሆንም ፣አረ አንዳንዴም ምን አገባችሁ ? ማለትም ያሳኛል ፣ታዲያ ልማደኛው አሰመሳይ አፌ የልቤን ሀሳብ ቀብሬ ፣ የነፍሴን ፍላጎት አፍኖ በቀደደዱለት ቦይ ይፈሳል።

#ታስሪያለው

ውብ አሁን

╭══•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀: ══╮
@tsihofoch
@tsihofoch
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ ══╯
256 views06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-01 13:49:14 መውደድ ስለምን ያስፈራል

*

*
ወደ መውደድ በቀረብን ወቅት ልባችን በሀሴት መሞላት በተስፋ መጓጓት ሲኖርባት በጭንቀት ትደክማለች መውደድ የስጋ ምቾት የነብስ ጥልቅ እርካታ የሕይወት ማጣጣሚያ ሁኖ እያለ
ስለምን መጥፎ እይታ ወይስ የልብ ስብራት እንዳይገጥመን እንሰጋለን

ደስታን የመቀበል ፍራቻ ደስታው የሚሰጠን ስሜት ሳንረዳ ሀዘኑላይ እንድናተኩር ማን ፈረደብን
ወደ መልካም መንደር እንድንመጣ ተጋብዘን ወደ ጥላቻ ከፍታ በስተት ሳይሆን በምርጫ አለክልከን ጫፍ ላይ እንቆማለን የወደድነው ወይም ተወዳጁ በመደሰት ሲጠብቀን ሲናፍቀን እኛ ያለንበት ቦታ በፍርሀት በስጋት ተውጠን መብላት መጠጣት መቀመጥ ተስኖን የወደድነውን ለመርሳት ከራሳችን ሙግት እንገጥማለን ለምን

መውደዳችንን ስለምን እንመራምራለን
የምርምሩም ውጤት ፍራቻ ይሆናል
ምርምራችንስ እንዴት ውጤቱ ፍራቻ ሲሆን አምነን እንቀመጣለን ለምን ብለን ፍራቻን አንቃወምም ተቃውመንም መውደዳችንን አምነን የግላችን አናረግም
ለምን

……………እሳቱ_ሰ

ውብ አሁን

╭══•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀: ══╮
@tsihofoch
@tsihofoch
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ ══╯
240 viewsedited  10:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-01 13:14:27 ሸረሪት እና እባብ

ወቅቱ የበአል ቀን እንደሆነ ቁልጭ ብሎ ከነምስሉ ይታየኛል።
በግምት የስምንት አመት ብሆን ነዉ። በወቅቱ ቤታችን የስክሪን መስኮት አልነበረም፤

ተሰብስበን ፏ ብለን እያየን ነዉ። በኋላ ላይ "ከእባብ እና ከሸረሪት ማን ያሸንፋል?" የሚል ጥያቄ ጋዜጠኛው ጠየቀ፦
ታዲያ የሁሉም ምላሽ ተመሳሳይ እና አጭር እባብ የሚል ነዉ(ከኔም ጭምር)

በኋላ ላይ ግን "አይደለም" የሚል አስገራሚ መልስ ሰነዘረ፥
(ምክንያቱን ለማወቅ በጉጉት ምን ያህል እንደተቁነጠነጥኩ እኔ ነኝ የማዉቀዉ፤)
"እንዴት እንደሆነ ለማወቅ ቀጣዩን መሰናዶ አይተን እንመለሳለን" አለ ጋዜጠኛዉ።

መሰናዶዉ በሰላምታ ጀመረ እያለ ቀጠለ "ጪዉ ጪዉ ጪዉ" የሚል ድምፅ ይሰማል።
ፅልመት ከጥቂት ብርሃን የሞሸረዉ ጥቁር ከ ሰማያዊ ለሊት ነዉ.....
.. እንጨት ላይ የሚሄድ ቀጭን ጠቃጠቆ ያለበት እባብ በቀስታ እየተጠማመዘ እየሄደ ነዉ(አካሄዱ ሲሰቀጥጥ)
ጋዜጠኛዉ ይተርካል "አሁን ደግሞ ሸረሪቱን እንመልከት" አለ (አይኔ ቀስት ሆኗል፤).................
...ትልቅዬ ሸረሪት በጎኑ እየተንጎማለለ በኩራት ይራመዳል (ብዙ እግር እንዳለዉ አላዉቅም ነበር)
ከዛ እንዴት እንደሆነ ብረሳዉም መተናኮስ ተጀማመሩ እባቡ ሊነድፈዉ መርዙን ረጅም ርቀት ይረጫል ፥

የሆነው ግን ሸረሪቱ ከእባቡ ጀርባ ላይ ተሰቀለ፣ በድሩ ዙርያውን መጠምጠም ጀመረ እያለ መርዙን የሚረጭበት አፉን ድረስ አከናነበዉ፤ ድሩን ሲጠልፍ እየደጋገመ በፍጥነት እና በጥንቃቄ ነዉ።

(እጅግ ተደንቂያለሁ)፦ ጋዜጠኛዉ ቀጠለ " አሁን ደግሞ እንዴት እባቡ እንደሚሞት እናያለን" ሲል ለወንበሩ የመጨረሻ ለመቀመጫዬ መጀመሪያ ላይ ነበርኩ፤ ቀጥሏል......

.....ሸረሪቱ ከእባቡ ጀርባ ተቆናጦ አፉን ሰክቶ ይሁን እንጃ እግሮቹ አየር ላይ ናቸዉ። እንደ መርፌ ደሙን እየወሰደበት ነዉ።
" አሁን መርዙን ጨርሶ ወስዶባታል ይሄ ማለት ሀይሉ እያለቀ ነዉ።" አለ

እባቡ ሲልፈሰፈስ ያስታዉቃል ሸረሪቱ አሁንም ላዩ ላይ ነዉ!
እየቆየ ሲሄድ እባቡ ወደ ነጭ ንፍጥ መሳይ ሙልጭልጭ ነገር ተጥለቅልቆ ወደቀ፤
ቀልድ ቢመስልም በሸረሪት አሸናፊነት ጦርነቱ ተጠናቀቀ፤
"ጉድ ጉድ ጉድ" ትላለች እቴቴ እኔ ግን ታዲያ ከዛ በኋላ ETVን ወደድኩት አይገልፀውም በተለይ በተለይ የበአል ፕሮግራም፤
ከዛ በኋላ የበአል ጊዜ ቲቪ ላይ ቀዳማዊት ተከታታይ ሆንኩኝ።
ለዛም ሳይሆን አይቀርም በበአል መባቻ ሪሞቱ ሲበላሽ ሳልሰስት 50 ብር የገዛሁት

ጊዜም እየነጎደ ከበአል በአል እየተተካ እድሜም እንደ እባብ እየተዥጎረጎረ ዛሬ ላይ ደርስኩና
ሸረሪት ባየሁ ቁጥር ያ ታሪክ ትዝ ይለኛል፤ ስለ እባብ ሲወሳም እንዲሁ ከሱ በበለጠ ግን በእዉቀቴ ልክ ከስኬት ጋር አያያዝኩት እሱም፦

የት ትደርሳለች? ተብላ የተናቀች ነፍስ ድል ስትጎናፀፍ፣ ማማዉን ስትረግጥ፤ የሀሜት እና የተንኮል መርዙን ሲረጩባት የስራ ፣የትጋት ድሯን ስትጠመጥም፤
መርዛቸው ስኬቷ ፊት ሲሸነፍ፣ ተልፈስፍሶ ሲወድቅ፣ የናቀ ሲከስም የተናቀ ሲጠቅም................ ብቻ ምኑ ቅጡ ብዙ ብዙ ይታየኛል።

እናማ.................
ህይወት በምሳሌ የተሞላች መልመጃ ናት።
የእባቡና የሸረሪቱ አይነት ታሪክ ደግሞ ለነፍሳችን ብርታት አንዳንዴ ታስፈልገናለችና አተኩረን እንያት።
ልክ ፈላስፋዉ እንዳለው "መማር የፈለገ በእንሰሳም ይማራል።"

በዚህ አጋጣሚ ግርግዳ ላይ አይተሃት በጫማ የጠለዝካትን ልጅ spiderዋ " አይ አለመተዋወቅ" ብላሃለች


………… ፈትሒያ

ስለ-ፅሁፉ ሃሳብ አስተያየት ካላቹ ፦ @Fethetulletiya
ይጠቀሙ………………


ውብ አሁን

╭══•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀: ══╮
@tsihofoch
@tsihofoch
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ ══╯
245 views10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-05-31 13:16:18 "ኑሮን ያስወደድከው አንተ ነህ!"

ከምሽቱ ሁለት ሰዓት አካባቢ ነው… ከኦሎምፒያ ወደ አጎና ሲናማ ለመሄድ በመከራ የተገኘች
ሚኒ ባስ ውስጥ ለመግባት ሰዉ ይጋፋል… ምንም እንኳን ታሪፉ 1ብር ከ35 ቢሆንም ረዳቱ

"ሁለት፣ ሁለት ብር ነው… ሰምታችኋል!"

እያለ እያስጠነቀቀ በተገኘው ክፍት ቦታ ተሳፋሪውን ይጠቀጥቃል… እንደምንም ብዬ ታክሲው ውስጥ ከገባሁ በኋላ… የረዳቱን ማስጠንቀቂያ ማንም ቁም ነገሬ አለማለቱ በጣም አስገርሞኝ ለረዳቱና አብሮኝ ለነበረ ጓደኛዬ በሚሰማ ድምፅ… "ለምን ሲባል!" ብዬ አጉረመረምኩ… ተሟግቼም… "አንተ ከማን ትበልጣለህ…"ተብዬም ለኔና ለጓደኛዬ 2ብር ከ70 ከፈልኩ…

እዛው ታክሲ ውስጥ ሳለን… ጓደኛዬን እንዲህ አልኩት… "ኑሮን ግን ማን እንዳስወደደብን
ታውቃለህ?" መልስ እስኪሰጠኝ አልጠበኩም… ንግግሬን ቀጠልኩ…

"ኑሮን ያስወደድነው እኛው እራሳችን ነን… አንተና እኔ!" ጓደኛዬ ጆሮውን ሰጠኝ… ቀጠልኩ…
"እዚህ ታክሲው ውስጥ ስንት አይነት ሰው ሊሳፈር እንደሚችል አስበኸዋል?"
"ለምሳሌ… ታክሲ ውስጥ ከተሳፈሩት አንዱ ዶክተር ነው እንበል… ይሄ ዶክተር ክሊኒክ
አለውም ብለን እናስብ… ታዲያ… ባለ ታክሲውና ረዳቱ ስለመሸ ብለው 65ሳንቲም እዚህ
ዶክተር ላይ ሲጨምሩበት… ዶክተሩ በተራው ወደ ክሊኒኩ ይገባና 50ብር የነበረውን የካርድ
ማውጫ ዋጋ ከሁለት ሰዓት በኋላ 60ብር ያደርገዋል… ምክንያቱም የታክሲ ዋጋ
ጨምሮበታላ!

ሌላም… የዳቦ ቤት ባለ ቤት የሆነ ግለሰብ እዚህ ታክሲ ውስጥ አለ እንበል… እሱም…
ምናልባትም… ከሶስትና አራት ዳቦ የሚያተርፋትን 65ሳንቲም በትራንስፖርት ላይ
ስለተጨመረበት እሷን ለማካካስ ሲል 1ብር የነበረውን ዳቦ 1ብር ከ10ሳንቲም ያደርገዋል…
ምክንያቱም የታክሲ ዋጋ ጨምሮበታላ!
አንዷ ደግሞ እንጀራ ሻጭ ናት እንበል… 2ብር ከ50 ትሸጥ የነበረውን እንጀራ 2ብር ከ75
ታደርገዋለች… ምክንያቱም የታክሲ ዋጋ ጨምሮባታላ!

ሌላው ደግሞ ባለ ሱቅ ነው እንበል… 25ብር የነበረውን የስኳር ዋጋ 26 ብር ያደርገዋል…
ምክንያቱም የታክሲ ዋጋ ጨምሮበታል!
እንዲሁም… ሌላኛው ተሳፋሪ ትምህርት ቤት አለው እንበል… ታዲያ ይሄ ግለሰብ… 150ብር
የነበረውን ወርሃዊ የትምህርት ቤት ክፍያ 160ብር ያደርገዋል… ምክንያቱም የታክሲ ዋጋ
ጨምሮበታል!

ሌላኛው… ባለ ስጋ ቤት ነው፣ ሌላው… ባለ ወፍጮ ቤት… ሌላው… እህል ነጋዴ… ሌላው…
አትክልት ነጋዴ… ሌላው… ባለ ምግብ ቤት… ሌላው… ጠበቃ… ሌላው… ጥበቃ… ሌላዋ
የቤት ሰራተኛ… ሌላም… ሌላም…
ታዲያ ባለታክሲውና ረዳቱ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ሆነው ሳሉ እነሱ በጨመሯት 65 ሳንቲም ምክንያት ህክምና ይጨምርባቸዋል፣ ዳቦ ይጨምርባቸዋል፣ እንጀራይጨምርባቸዋል፣ ስኳር ይጨምርባቸዋል… ሌላም… ሌላም…
ሾፌሩና ረዳቱ ዛሬ ማታ የለኮሷት ትንሽ ክብሪት ሌሊቱን ሙሉ ስትቀጣጠል አምሽታ… አንዱ፣
ለሌላው እያቀበላትና እየተቀባበላት አድራ በነጋታው ሰደድ እሳት ሆና እነሱኑ ትፈጃቸዋለች፡፡

የሚገርመው ነገር… ባለታክሲው ትርፍ የጫናቸውን ጨምሮ በአጠቃላይ 20 ሰዎችን ጭኗልእንበል… ታዲያ በ65ሳንቲሟ ተሰልቶ ዛሬ ማታ 13ብር አትረፎ ሊሆን ይችላል… ነገር ግን…
በንጋታው… ከላይ ከጠቅስኳቸው፣ እሱ እራሱ ከሚጠቀማቸው አምስት አገልግሎቶች ብቻ
21ብር ከ35ሳንቲም ተጨማሪ ሊከፍል ግድ ይሆንበታል ማለት ነው፡፡

ወንድሜ ሆይ! ኑሮ ተወደደ እያልክ እያማረርክ ነው? እኔ ግን አንድ ነገር ልንገርህ… ኑሮን
ያስወደደው ማንም ሳይሆን… አንተው እራስህ ነህ!

አንቺ እህቴስ! ኑሮ ንሮብሻል? እንግዲያውስ አንድ ነገር ልምከርሽ… ኑሮሽ የተወደደው አንቺ
በወደድሽው ልክ ነው… አንቺ በመረጥሽውና በፈቀድሽው ልክ… ኑሮሽ የተወደደው ያለ በቂ
ምክንያት 70ሳንቲም ሳታንገራግሪ የጨመርሽ ጊዜ ነው… ኑሮሽ የተወደደው የጋገርሽው
እንጀራ ላይ ያለ አግባብ ዋጋ የጨመርሽ ጊዜ ነው… ኑሮሽ የተወደደው የጋገርሽው አምባሻ
ላይ የተጋነነ ዋጋ የጨመርሽ ጊዜ ነው… ኑሮሽ የተወደደው ከጓሮሽ ያበቀልሽው ጎመን ላይ
የማይገባ ዋጋ የጫንሽ ጊዜ ነው…

አንተ ኑሮ የተወደደብህ፣ አንቺ ኑሮ የተወደደብሽ… ያልተረዳኸው፣ ያልተረዳሽው ነገር ቢኖር ህይወት የቅብብሎሽ ሰንሰለት መሆኗን ነው… ኑሮ የገዢና የሻጭ፣ የአገልግሎት ሰጪና ተቀባይ ቀለበት መሆኗን ነው… ታዲያ! ዛሬ በሌላው ላይ የወረወ ርከው ጠጠር ነገ ከሌሎች ጠጠሮች ጋር ተዳም ሮ አንተ ላይ ከባድ አለት ሆኖ ይመጣብሃል… የማትሸከመው ቀንበር ይሆንብሃል… አንገትህን ያስደፋሃል… አንተ ዛሬ የከፈትካት ቀዳዳ ነገ በሌሎች ሰፍታ የአውሬዎች ሲሳይ ታደርግሃለች… አንተ ዛሬ የፈጠርካት ጠብታ ነገ ጎርፍ ሆና ይዛህ
ትሄዳለች…

ታዲያ ያኔ ማን ላይ ልታላክክ ነው? መንግስት ላይ? ባለ ሃብት ላይ? ነጋዴ ላይ? ገበሬ ላይ?
እኔ ግን ልምከረህ… የመንግስትም፣ የነጋዴም፣ የገበሬም፣ የመምህርም፣ የአስተማሪም፣
ስልጣን ሰጪና ነፋጊ አንተ ነህ! ማንም የሚገዛህም ሆነ የሚሸጥልህ አንተ በሰጠኸው ዋጋና ተመን ልክ ነው፡፡ እሱ ያወጣው ዋጋ ካልተስማማህ እያጉረመረምክ አትግዛ! ይልቁንም በኢትዮጲያዊ ቆራጥነት ቆፍጠን ብለህ… "አልገዛህም!" በለው ያኔ እሱም የሚገዛው ነገር አለና ብር ስለሚያስፈልገው አንተ በተመንክለት ዋጋ ይሸጥልሃል… ምናልባት… ዛሬ የተጣለችብህን ጭማሬ የመግዛት አቅሙ ስላለህ ከመጨቃጨቅ ብለህ ጭማሬዋን ከፍለህልትሄድ ትችላለህ… ነገር ግን ካንተ በታችያለውንወንድምህን ደግሞ አስብ!አንተ ዛሬ ለደካማው ወንድምህ ዘብ ካልቆምክለት፣ ነገ ትላንትየናቅካት ጭማሪ አንተው ላይ እጥፍ ሆና ስትመጣብህ ማን ከጎንህ ሊቆም ነው? ስለዚህ… አንድ ነገር ተረዳ…

የማንኛውም ነገር አስጨማሪም ጨማሪም አንተ ነህ! ኑሮህን ያስወደድከው አንተው እራስህ ነህ!

ቢንያም ሀብታሙ

ውብ አሁን

╭══•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀: ══╮
@tsihofoch
@tsihofoch
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ ══╯
223 views10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-05-31 06:43:19 ጨለማ ያልተዘመረለት ብርሃን ነው

ሲመሽ ደስ ይለኛል!.........ፀሐይቱ ካድመሱ ባሻገር ካለው ኮሮጆዋ ስሰምጥ .....ሁለንተናው በፅልመት ሲፈካ........ብርሃን ጠፍቶ ጨለማው ሲያበራ ሀሴት ይሰማኛል ....ምናልባት ድቅድቁ ፀፀት ያጎበጠውን ልቤን ከፀፀቴ የሚጋርድልኝ መስሎኝ ይሆን? እኔንጃ!

ውድቀቱ ምችት ይለኛል ሁሉም ፀጥ ብሎ ግን ሁሉም ሲለፈልፍ .........ሁሉም ጭፍን አርጎ ግን ሁሉም ሲመለከት .........ሁሉም ግድም ብሎ ግን ሁሉም ሲራኮት ......ስጋዎች ሞተው ነፍሶች ሲነቁ ..........ስጋዎች ፀጥ ሲሉ ነፍሶች ካለም ጥግ እስከ አለም ጥግ በህልም ሰረገላ ሲጓዙ ፣ ላይሰራ ሲያቅዱ ፣ ላይዋጥ ሲጎርሶ ፣ ላይሰማ ሲያወጉ ፣ ላይታወስ ሲያነጉ...............እሄን ሁሉ የነፍስ አለም ፣ በጨለማው አሻግሬ ፣ በአየሩ ላይ በርሬ ፤ በምድርም ስር ሰግሬ ......የዝምታን ህጋቸውን ሳልሰብር የመርጋትን ደንባቸውን በማክበር ፀጥታ በተከናነበ እርጋታ እንደተጀቦንኩኝ ሀሳባዊውን አለም በእውኑ እኔነቴ ስጋተው ፣ ደስታ ቃሉ ያንስብኛል ብቻ ሲመሽ ደስ ይለኛል።

ለሊቱ የፀሐይን ነጭ ጨለማ በጥቁር ብርሃኑ ሲንደው bravo! ይላል ውስጠቴ ........ ያንን የሁሉን ጠባሳ ካላሳየው ከሚለው ቀን በኋላ ጠባሳ የለኝም የሚያስብል ተስፋም ኩራትም የሚያጎናፅፈው ማታ ሲመጣ ኋጢአተኛዋ ነፍሴ እስኪነጋም ቢሆን ትፀድቃለች ......እስኪጠባም ቢሆን ትሽራለች......አይኖች እስኪነቁም ቢሆን በጨለማው ስብራቷን ሰውራ ፣ አይን በለለበት ቢኖርም በማያይበት ከፈካው ጨለማ አብራ ትፈካለች።

...................................ነጋ መሰል


ስለ ፅሁፉ ሃሳብ አስተያየት ካላቹ @Deathman74 ይጠቀሙ !!!


ውብ አሁን

╭══•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀: ══╮
@tsihofoch
@tsihofoch
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ ══╯
223 views03:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-05-30 15:34:53 ፍት-ፍት

"ቋቋቋቋ" የሚል የተለምዶ ድምፅ እያጀበኝ ነዉ። ግን ከዛ በላይ ወደፊት ለፊቴ ያለዉ ምግብ ቤት ትኩረቴን ስቦኝ እያመራሁ ነዉ።
የዛሬው ደግሞ አጃኢብ ነዉ። ጭራሽ "እኔ የምበላው ፍትፍት እዉቅና አግኝቶ ህዝብ መብላት ጀመረዉ?
ከወደ ላዬ ፊት ለፊት ያለዉ ታፔላማ የመግባት ጉጉቴን ጨማመረዉ፤
ልክ ስገባ ብዙ ሰዎች ጣዉላ መሳይ ወንበር እና አጠር ያለች ጠረጴዛ ነገር ላይ ነጭ የበዛዉ ነገር እያጣጣሙ ግማሾቹ እየተገረሙ ይበላሉ፤ አንዳንዱማ ከነ ቤተሰቡ ነዉ የመጣዉ እናት ልጆች ከነ ባለቤትየዉ፤
የኑሮ ዉድነት የገባዉ ምግብ ቤት ሳይሆን አይቀርም አልኩ ወደ ዉስጥ፤

እኔም በአቅራቢያዬ ወዳገኘሁት ወንበር ጠጋ ብዬ ተቀመጥኩኝ እጁን ከበስተኋላው አጣምሮ ትንሽ ሸብረክ ብሎ ፈጣን የሚመስል ልጅ ብቻውን ያስተናግዳል፥ በወዲያኛው ስፍራ የሚሰሩ አንድ ሶስት ሰዎች ይታዩኛል፥ የሚያበስሉት ይሆናሉ አልኩኝ፤

ተራዬ እስኪደርስ ቤቱን ዙርያውን ስቃኝ የቤቱ ቀለም ግራ ያጋባል የሆነ የተጠበሰ ነገር ይመስላል፣የበሰለ እንጨትም ይመስላል ግን በአጠቃላይ ዜግነት የሌለው ቀለም ነዉ።(ቀለምም ዜግነት አለዉ እንዴ?)
ድንገት ወደ ታች ሳይ ደፍተር ነገርዬ ተከድኖ ተቀምጧል "ሜኑ መሆኑ ነዉ"አልኩ
ገና አንብቤ ሳልጀምር ልጁ መጥቶ አጣደፈኝ
"አቤት ምን ልታዘዝ?"
"ምን ምን አላችሁ"
"ሁሉም"
"እሺ ልምረጥ" ወዲያው ተሰወረ ማንበብ ቀጠልኩ፣
"አንደኛ፦ነጭ ፍትፍት እንጀራ ጨዉ በዉሀ
ሁለተኛ፦ ግማሽ ሽንኩርት በአንድ ቲማቲም እንጀራ ለብለብ"
ሶስተኛ፦እንጀራ ቆረጥ ቆረጥ ቃሪያ ከተፍ ከተፍ በጨዉ በዉሀ
አራተኛ እያለ እያለ እስከ አስር ይሄዳል
አይኔን አፈጠጥኩ ሳቄ ካልሳከኝ ብሎ እያስቸገረኝ "ቡፍፍ" ብሎ በፍቃዱ ተሳቀ
አስተናጋጅ አልኩ እጄን እያጨበጨብኩ
"አቤት ጌታዬ" አለኝና በእጁ ቃሪያ ና ነጭ ሽንኩርት የተከተፈ በትናንሽ ሰሀን ይዟል
"እ ያላችሁ ምግብ ከፍርፍር ዉጪ የለም እንዴ?"
"አዎን" እየተሽቆጠቆጠ
"ለምን?" በአግራሞት ጠየኩ
"ጌታዬ ህጋችን ስለሆነ ነዉ ለየት ለማለት"
"እንዴት"
በአንድ እጁ የአፉን ጥጋ ጥግ እየጠራረገ በሞራል ቀጠለ
" እ አየህ የኛ ቤት ስትገባ እራሱ ታፔላዉ "ተመገቡ ነጭ ፍትፍት ለጤና ምግብ ቤት ነዉ።" (ረዥሙ የምግብ ቤት ስም ሳይሆን አይቀርም) እያልኩ ማሰብ ጀመርኩ
"እሺ" አልኩት እንደመባነን ብዬ
"ጨረስኩ እኮ"
"ይቅርታ ትደግምልኝ?"
"ጌታዬ ለየት ለማለት ነዉ ፍትፍት ቤት የከፈትነዉ ሀሳቡም የመጣዉ የባለቤቱ ባለቤት ፍትፍት ትወድ ነበር ነፍሷን ይማርና እና ባልተቤቱ እሷ ዘወትር አሰራሩን እየቀያየረች የምትሰራለትን ነጭ ማዕድ አንድም ለራሱ ሁለትም ለወገን ላስመግብ ብሎ ሶስትም ለየት ያለ ነገር እያለ ህዝቤ ስለሞተ ነፍስ ልዝራበት ብሎ ነዉ።"

ሲያወራ ፈጣን እና የተንዛዛ መሆኑንም አልታዘብኩም ነበር እንደ "ኧረ ኢሚኒየም" አልኩ በሆዴ ... ራፐር ዘፈን የሰማሁ መሠለኝ
"እሺ እና ለኔ ባንተ ምርጫ የቱ ይሁንልኝ" አልኩ እየፈገግኩ የሌለ ገርሞኛል
እሱም እየፈገገልኝ "ዘጠነኛ ላይ ያለዉ እንጀራ cut cut" አለኝ
"ጎሽ"አልኩ ሳቄን መቆጣጠር እቅቶኝ ተንከተከትኩ "ምነኛ ነዉ ደግሞ"
"ኢንግሊሽ በአማርኛ"
"እሱ ገባኝ ምክንያቱ ማለቴ ምንድነው አሰራሩ"
"እሱን ሳመጣዉ ታየዋለህ"
"ይሁን" አልኩ እጄን አገጬ ላይ አንተርሼ

"በወርቃማ ፕላስቲክ" ሰሀን ዙርያዉ ነጭ የተቆራረጠ እንጀራ እና በመሀሉ በርገር መሳይ የተጠበሰ ስጋ ዙርያውን በቃሪያና በነጭ ሽንኩርት(የደቀቀ) አጠገቡ ፍትፍት አለ
በሱ ተገርሜ ሳልጨርስ አጓት በቀላስ እና ሚጥሚጣ አመጣልኝ
"ይሄኔ ነዉ መሸሽ" አልኩ ደንግጬ
"ትወደዋለህ ጋሼ አንደኛ ነዉ" አለኝ አዉራ ጣቱን ከሌባ ጣቱጋ ክብ ሰርቶ
"እስቲ" አልኩ ግርምት ሳቅ ፍርሃት ስሜቶች እያጣደፉኝ ለደቂቃዎች ሁሉንም ማየት ጀመርኩ "የምን ጉድ ነዉ? በብላሽማ አልወጣም" ብዬ እጄን ሰብሰብ አድርጌ ቀመስኩት እዉነት ለመናገር ተገረምኩ እንደዚህ የሚጣፍጥ አልመሠለኝም አፌን እየመጠጥኩ ሳለዉ
"አንተ የሞትክ ተነሳ እንጂ" የሚል ድምፅ እንደ ገደል ማሚቱ ያስተጋባል!
"ቆይ አንዴ ልብላ" አልኩ
"መቼ ተነስተህ" መለሰልኝ "ኡፋፋ" አልኩ በብስጭት
"ቿህ"የሚል ድምፅ ስሰማ በረገግኩ ለካስ ዉሀ ላዬ ላይ ተደፍቶ ነዉ።
ዙርያ ገባዬን አፍጥጬ አየሁ የታለ ምግብ ቤቱ? ፍትፍቱስ?አጓቱስ?.... "ቅዠታም ያንተዉ ደግሞ ማቆሚያም የለዉ እቴ በል ተነስ እና ብላ"
"ዛሬም ነጭ ፍርፍር?" በሰልችት ቢያንስ cut cut አይደለ
"እዉይይ እና ምን ይሁንልሽ ማሙሹ"
"እንጀራ ከት ከት"
"ምኑን አመጣህ ደግም የምን ክት ክት ነዉ? ያንከትክትህ እቴ ሆሆይይ" አለች አሽሟጣ እየሳቀች
"እኔም አልሃለሁ ህልም የኑሮ ዉጤት ነዉ። ህልም ደግሞ የሃሳብ ዉጤት አል-ጣፋጭ የሆነ ሀሳብ ምግብ....ሲሆን ደግሞ ቅዠት" ቅዠት ወደ እዉን ሲተረጎም ደግሞ ፍት-ፍት ይሆናል።(ቅዠታዊ ፍልስፍና )
ዳይ ወደ ፍት-ፍት

………… ፈትሒያ

ስለ-ፅሁፉ ሃሳብ አስተያየት ካላቹ ፦ @Fethetulletiya
ይጠቀሙ………………


@tsihofoch
@tsihofoch
224 viewsedited  12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-05-29 18:13:45 --- ሽማግሌው

---- ግሩም ተበጀ

ገና በጠዋቱ --- 2 : 30 ላይ . . . ክሊኒካችን በህ
መምተኛ በተጨናነቀበት ወቅት ነበር አንድ አረጋ
ዊ ወደ ክሊኒካችን የገቡት። በግራ ክንዳቸው ላይ
የቁስል እሽግ ይታያል። በግምት 70 ዓመት የሚ
ሆናቸው አዛውንት ናቸው። በቀስታ አግዳሚው
ወንበር ላይ ተቀምጠው ሰዓታቸውን ማየት ጀመ
ሩ። የቸኮሉ ይመስላሉ።

"ምን ልርዳዎት" አልኳቸው።

የቀስሉ እሽግ እንዲቀየርላቸው ነው የመጡት።
ከ30 ደቂቃ በኃላ ግን ቀጠሮ ስላላቸው ቸኩለዋል

በህክምና ሊያገኙ የሚችሉት ገና ከ1 ሰዓት በኃላ
እንደሆነ ይገባኛል።ምን ማድረግ እችላለሁ! ግን
እስቲ ቢያንስ ቁስሉን ፈትቼ ልየው ብዬ እሽጉን
ስፈታው ቁስሉ ደርቋል።

በጣም ጥሩ!

ከአንዱ ዶክተርጋ ተነጋገሩክ።አስፈላጊውን መድኃ
ኒቶችና የህክምና የህክምና ቁሳቁሶች ወስጄ ህክ
ምናውን አከናወንኩላቸው። አረጋዊው ወደ ቀጠሯ
ቸው በጣም በመቸኮላቸው ምክንያት ትዕግስት
አጥተዋል።አሁንም የሚያዩት የእጅ ሰዓታቸው
ቁስሉ ያለበት ግራ ክንዳቸው ላይ ነው ያለው።
ስለዚህ እንዴት ሰዓታቸውን ይዩ . . .። ቁስሉን እየ
ፈታሁላቸው እሳቸው አሰግገው ሰዓታቸውን ለማየ
ት ይጣጣራሉ።

"ለመሆኑ ይሄ ያህል የቸኮሉበት ቀጠሮዎት የት
ነው . . ."አልኳቸው እንደ ጨዋታ ያህል።

"3 : 00 ሰዓት ላይ ከባለቤቴ ጋር ቁርስ ለመብላት
ቀጠሮ አለኝ" አሉኝ።

"አሀ . . ."

ቁስላቸውን መልሼ አያሸግኩላቸው አረጋዊው ታሪ
ካቸውን አጫወቱኝ። እንዳሉኝም እንዲህ የቸኮሉት
ከሚስታቸው ጋር 3 : 00 ሰዓት ላይ ቁርስ የመ
ብላት ቀጠሮ ስላላቸው ነው። ሚስታቸው ግን
ቤት አይደለም ያሉት።ህመምተኛ ናቸው። ሆስፒታ
ል ነው ያሉት።

"ባለቤትዎ ሀይለኛ ሴት ናቸው ማለት ነው . . ስለ
ዚህ ነው ላለማርፈድ ይሄን ያህል የቸኮሉት" አልኳ
ቸው።

"አይ . . . እሷ እንኳን ምንም አትለኝም"አሉኝ አረጋ
ዊው ፤ "እኔው ነኝ . . "

"እንዴት . . ." አልኳቸው እንዲጫወቱ ፈልጌ።

"አይ ልጄ ፣ ባለቤቴማ ላለፉት አምስት ዓመታት
አልዛይመር በተባለ የመርሳት በሽታ ተይዛ ባለቤ
ቷ እንደሆንኩ እንኳን አታውቅም" አሉኝ ትክዝ ብለ
ው።

ገረመኝ። አረጋዊው ላለፉት አምስት አመታት አን
ድም ቀን ሳያስተጓጉሉ ሆስፒታል እየሄዱ ከባለቤ
ታቸው ጋር ቁርስ ቆርሰዋል።ባለቤታቸው ግን
እያንዳንዱን ቀን ከተለያየ ሰው ጋር ቁርስ እንደበሉ
ነው የሚያውቁት።

ግማሽ ምዕተ ዓመት በዘለቀው ትዳራቸው . . .
የትዳር አጋራቸው የሆኑትን ባለቤታቸው ፈፅሞ
ረስተዋል። ምስኪኑ አረጋዊ ግን ሁልቀን ሳያረፍዱ
ሆስፒታል እየተገኘ ጨርሶ ከማያስታውሷቸው ባለ
ቤታቸው ጋር ፍቅርን ይቆርሳሉ።


@tsihofoch
@tsihofoch
205 views15:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ