#MoE የእስልምና እምነት ተከታይ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የመውሊድ በዓልን አክብረው መስከረም 29/2015 ዓ.ም ወደተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ መግባት ይችላሉ ተብሏል። ይሁን እንጂ መስከረም 28/2015 ዓ.ም የመውሊድ በዓል መሆኑን ተከትሎ፤ የእስልምና እምነት ተከታይ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች በዓሉን አክብረው መስከረም 29/2015 ዓ.ም መግባት እንዲችሉ የተፈቀደላቸው መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል። በዚህም ተፈታኞቹ እሁድ መስከረም 29/2015 ዓ.ም ጠዋት ወደተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ በመግባት ከሰዓት ስለፈተናውና ተያያዥ ጉዳዮች በየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ገለጻ እንደሚደረግላቸው ሚኒስቴሩ ገልጿል። @TMIHIRT_MINISTER @TMIHIRT_MINISTER 877 viewsedited 15:41